Your trial period has ended!
For full access to functionality, please pay for a premium subscription
SP
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
https://t.me/sputnik_ethiopia
Channel age
Created
Language
Amharic
0.57%
ER (week)
15.96%
ERR (week)

ያልተነገረውን እንነግርዎታለን

ስለ አፍሪካ በእንግሊዘኛ ቋንቋ፤ @sputnik_africa

Messages Statistics
Reposts and citations
Publication networks
Satellites
Contacts
History
Top categories
Main categories of messages will appear here.
Top mentions
The most frequent mentions of people, organizations and places appear here.
Found 2 601 results
ኢትዮጵያ ፋሺዝምን የመከተችና ድል ያደረገች ቀዳማዊ ሀገር፦ ክፍል 2

'ሞሶሊኒ በኢትዮጵያ እጅግ ተበሳጭቶ ነበር'

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሕበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት ያነሱት ነው።

🗣 "ማሸነፍ እችላለሁ፤ ፋሺስቶችን ከሀገሬ ማስወጣት እችላለሁ፤ ያለምንም እርዳታም ቢሆን" የሚለው ጠንካራ ስሜት ኢትዮጵያውያን በሞሶሊኒ ጦር ላይ ድል እንዲቀዳጁ አድርጓቸዋል ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 18:15
t.me/sputnik_ethiopia/8896
#viral | ከየመን የባሕር ዳርቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ በጎች ከመስጠም ተረፉ

በምዕራብ የመን የባሕር ዳርቻ ባብ ኤል-መንደብ ባሕረ ሰላጤ በመቶዎች የሚቆጠሩ በጎችን የጫነ ጀልባ የመስጠም አደጋ ላይ እንደነበር ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 18:12
t.me/sputnik_ethiopia/8895
የሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ አስከሬን ሮም በሚገኘው ሳንታ ማሪያ ማጆሬ ባዚሊካ በክብር አርፏል ስትል ቫቲካን ገለፀች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 17:03
t.me/sputnik_ethiopia/8894
🇪🇹 የኢትዮጵያ መንግሥት ገቢ 134 በመቶ ብልጫ እንዳስመዘገበ ተገለፀ

ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ትናንትና ዛሬ ካካሄደው መደበኛ ስብሰባ በኋላ መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ያለፉት 9 ወራት ጠቅላላ የመንግሥት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የ134 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን ገልጿል።  የውጭ ብድር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 13.7 በመቶ ወርዷል፡፡

ፓርቲው የውጭ ምንዛሬ ክምችት ዕድገት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ203.99 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብሏል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነቱ እየጨመረ መምጣቱም ተጠቅሷል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 16:52
t.me/sputnik_ethiopia/8893
የድል መሳሪያዎች - በዘይት እና በባሩድ የተነከረ። በእሳት እና በብረት የተወለደ - "ሁሉም ነገር ለጦር ግንባር! ሁሉም ነገር ለድል!" መሬት፣ አየር፣ መድፍ - ብረት ብቻ ሳይሆን የታላቁ ጀብድ ጸጥ ያሉ ምስክሮች ናቸው!

ስፑትኒክ የጦርነቱን ጀርባ የሰበሩ የድል ጦር መሣሪያዎችን በ3D ሞዴል ያቀርብሎታል።

▶️ በዚህ ከፍል የማይበገረው "ክሊም ቮራሺሎቭ"፦KV-1

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 16:15
t.me/sputnik_ethiopia/8892
📹 የ"ሴቨር" የጦር ቡድን በኩርስክ ክልል በዩክሬን ጦር ነጻ በወጣው የመጨረሻ መንደር በሆነችው ጎርናል የሩሲያን ባንዲራ ሰቀሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 15:51
t.me/sputnik_ethiopia/8891
የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም በኩርስክ ክልል የዩክሬን ወታደሮች ሽንፈትን በተመለከተ ካቀረቡት ሪፖርት ዋና ዋና ነጥቦች፦

🔹የጄራሲሞቭ ቁልፍ መግለጫዎች፦

◾️ በኩርስክ የገቡትን የዩክሬን ኃይሎች ለማስወጣት የተካሄደው ዘመቻ ተጠናቋል። በክልሉ የመጨረሻው ጎርናል መንደር ዛሬ ቅዳሜ ነፃ ወጥቷል።

▪️ በኩርስክ ነፃ በወጡ አካባቢዎች ለመደበቅ እየሞከሩ ያሉትን የዩክሬን የጦር ኃይል ወታደሮች ለመለየት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።

▪️ የዩክሬን የጦር ኃይሎች በኩርስክ ከ76 ሺህ በላይ ወታደሮቹን በሞትና በጉዳት አጥቷል።

▪️ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጦር ጋር በመሆን በጀግንነት ተዋግተዋል።

▪️ በሱሚ ክልል የፀጥታ ቀጣና ማቋቋም ቀጥሏል። አራት መንደሮች ነፃ የወጡ ሲሆን ከ90 ካሬ ኪ.ሜ በላይ መሬት በቁጥጥር ሥር ውሏል።

▪️ በኩርስክ የሚገኙ 19 መንደሮች ሙሉ በሙሉ ከፈንጂዎች ነጻ ሆነዋል።

🔹የፑቲን ቁልፍ መግለጫዎች፦

▪️ በኩርስክ የጠላት ሙሉ ሽንፈት በግንባሩ ሌሎች ወሳኝ ቦታዎች የሩሲያ የጦር ኃይሎች በቀጣይነት ስኬታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ሁኔታዎችን ያመቻቻል።

▪️ የኪዬቭ አገዛዝ "ቁማር" ሙሉ በሙሉ ከሽፏል።

▪️ የኩርስክ ነፃ መውጣት የኪዬቭን ኒዮ-ናዚ አገዛዝ ሽንፈት ያፋጥናል።

▪️ ፑቲን በኩርስክ ውጤታማ የነበሩትን የሩሲያ ጦር ክፍሎችን አመስግነዋል።

▪️ ኩርስክን ነፃ ላወጡ የሩሲያ ወታደሮች ጀግንነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 15:34
t.me/sputnik_ethiopia/8890
ይመልከቱ| ፑቲን ኩርስክ ክልል ከዩክሬን ነጻ መውጣቱን አስመልክቶ ያደረጉት መሉ ንግግር

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 15:31
t.me/sputnik_ethiopia/8889
❗️ሩሲያ ሰሜን ኮሪያ በኩርስክ ክልል ዩክሬንን ለማስወጣት ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና አቀረበች

የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በኩርስክ ክልል ከሩሲያ ኃይሎች ጋር በመሆን ጥንካሬና ጀግንነት አሳይተዋል ሲሉ የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ቫለሪ ጄራሲሞቭ ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 14:50
t.me/sputnik_ethiopia/8888
❗️ ፑቲን የኩርስክ ክልል ነፃ መውጣት የኪዬቩን የኒዮ-ናዚ አገዛዝ ሽንፈት ያፋጥናል አሉ

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ተጨማሪ መግለጫዎች፡-

▫️ የኪዬቭ አገዛዝ "ቁማር" ሙሉ በሙሉ ከሽፏል።

▫️ የሩሲያ ወታደሮች የኩርስክ ክልልን ነፃ በማውጣት ላሳዩት ጀግንነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 14:45
t.me/sputnik_ethiopia/8887
💥 ፔንታጎን ፍሎሪዳ ውስጥ ሚስጢራዊ የሚሳኤል ማስወንጨፍ ሙከራ አካሄደ

በቅርቡ በኬፕ ካናቨራል ተደርጓል የተባለውና በማሕበራዊ ሚዲያ የተጋራው ቪዲዮ የአሜሪካ የመከላከያ መሥሪያ ቤት ሙከራ እንደነበር ተረጋግጧል።

ፔንታጎን የረዥም ርቀት ሃይፐርሶኒክ መሣሪያውን "ጥቁር ንስር " ብሎ ሰይሞታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 14:15
t.me/sputnik_ethiopia/8886
ደ ጉል፤ መጪውን ግዜ ለመገንባት ታሪክን መጠበቅ፦ ክፍል 4

የጄነራል ደ ጉል የወንድም ልጅ ሎረን ደ ጉል ናዚዝም ስላደረሰው የስሜት ቀውስ ይናገራሉ።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 14:15
t.me/sputnik_ethiopia/8885
❗️ክሬምሊን የሩሲያን ኩርስክ ግዛት ከዩክሬን ወታደሮች ነፃ የማውጣት ዘመቻ እንደተጠናቀቀና ፑቲን ሪፖርቱ እንደደረሳቸው አስታወቀ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 13:47
t.me/sputnik_ethiopia/8884
ትራምፕ ሩሲያ ነፃ ያወጣቻቸውን አካባቢዎች ተቆጣጥራ መቀጠሏን በተመለከተ የያዙት አቋም "የማይለወጥ" መሆኑን አንድ ዘገባ አመላከተ

ዶናልድ ትራምፕ ዘለንስኪ ግጭቱን ለመፍታት የልዩ መልዕክተኛቸውን ሀሳብ ከመቀበል 'በስተቀር ሌላ ምርጫ የለውም' ብለው እንደሚያምኑ ለስቲቭ ዊትኮፍ ቅርብ የሆኑ ምንጭን ጠቅሶ አንድ የብሪታንያ ጋዜጣ ዘግቧል።

ምንጩ እንዳሉት ዋሽንግተን ኪዬቭ የማትስማማ ከሆነ ግጭቱ ለወራት ወይም ለዓመታት ሊቀጥል እንደሚችል ገልጻለች።

ትራምፕ ግጭቱን ለማቆም በሚደረገው ስምምነት ክራይሚያ የሩሲያ አካል ሆና ትቀጥላለች ሲሉ ቀደም ሲል አስታውቀዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡት አስተያየት 'ከሞስኮ ጋር ሙሉ በሙሉ የሚጣጣም ነው' ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 13:33
t.me/sputnik_ethiopia/8883
04/26/2025, 13:11
t.me/sputnik_ethiopia/8882
የሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በቫቲካን ተጀመረ

የጳጳሱን አስከሬን የያዘው ሳጥን ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ተወስዷል።

የስፑትኒክ ጋዜጠኛ እንደዘገበው በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በግምት 200 ሺህ ሰዎች ተገኝተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 13:11
t.me/sputnik_ethiopia/8881
❗️ በታስኒም የዜና ወኪል ዘገባ መሰረት በደቡባዊ ኢራን ወደብ ባንዳር አባስ ከፍተኛ ፍንዳታ ተከስቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 12:59
t.me/sputnik_ethiopia/8880
🇪🇹🇸🇴 ለሶማሊያ ሰላም እና መረጋጋት የአፍሪካውያን የጋራ ትብብር ወሳኝ እንደሆነ ኢትዮጵያ አስገነዘበች

በአፍሪካ ሕብረት የድጋፍና የማረጋጋት ተልዕኮ በሶማሊያ ሥር ወታደሮች ያዋጡ ሀገራት የሰላም አስከባሪ ኃይሉን ቁጥር በትንሹ በ8 ሺህ ከፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በአጋንዳ የተካሄደውን ስብሰባ ተከትሎ ባወጡት የጋራ መግለጫ በሶማሊያ እየጨመረ የመጣው የደህንነት ስጋት በሀገሪቱ ስርዓት በመመለስ ረገድ የተገኘውን ስኬት እንዳያከሸፍ መተባበር እንደሚገባ አስረግጠዋል።

በጉባዔው የኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ጂቡቲ እና ሶማሊያ የመከላከያ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 12:57
t.me/sputnik_ethiopia/8879
🌍 አፍሪካ ፣ ልዩ ምርጫ ፡ ይህን የመልዕክት መለዋወጫ 'ፎልደር' ከአህጉሪቱ አዳዲስ ዜናዎች ከሚገኙበት ቻናሎች ላይ ይጨምሩት ⤵️

👉👉 https://t.me/addlist/lwYcxR-tjCBiODBi 👈👈

#ad
04/26/2025, 12:10
t.me/sputnik_ethiopia/8878
1
1
289
ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር የምታካሂደው ውይይት እስኪያበቃ ድረስ በሚስጢር ትይዛለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ተናገሩ

"ከሌሎች በተቃራኒው በድርድር ላይ የምንወያየውን በይፋ አንናገርም። እንዲያ ካልሆነ ድርድሮች ቁም ነገር አይኖራቸውም" ሲሉ ሰርጌ ላቭሮቭ የሰላም ድርድሩን ዝርዝር ጉዳዮች በተመለከተ ለሲቢኤስ ኒውስ ተናግረዋል።

የሩሲያው ከፍተኛ ዲፕሎማት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በበኩላቸው "ከማንኛውም ሰው ጋር ከፕሬዝዳንት ትራምፕም ጋር ጭምር በየመገናኛ ብዙሃኑ ለማውራት ፈቃደኛ ናቸው" ብለዋል።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬን ግጭት በአደባባይ አይፈታም ሲሉ ቀደም ብለው ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 11:48
t.me/sputnik_ethiopia/8877
4
2
575
ትራምፕ በዩክሬን ጉዳይ "በዋና ዋና ነጥቦች" ስምምነት ላይ መደረሱን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በ "ትሩዝ ሶሻል" ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ ሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ "በከፍተኛ ባለ ስልጣናት ደረጃ " መደራደር አለባቸው ብለዋል።

ትራምፕ የሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመታደም አርብ አመሻሽ ሮም ደርሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 11:02
t.me/sputnik_ethiopia/8876
ሶስተኛው ዙር የአሜሪካ-ኢራን የኒውክሌር ውይይት ዛሬ በኦማን ይጀመራል

የኢራን የዜና ወኪል ዋይጄሲ እንደዘገበው የአሜሪካው ቡድን ቅዳሜ ጠዋት ኦማን የደረሰ ሲሆን በመጀመሪያ የኦማን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርን ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አርጋቺ እና የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ተወካይ ስቲቭ ዊትኮፍ ድርድሩን ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ከድርድሩ በፊት በትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ "ሌላው ወገን [አሜሪካ] ፍትሃዊ እና ተጨባጭ ስምምነት ላይ ለመድረስ ምን ያህል ቁርጠኛ እና ዝግጁ እንደሆነ እናያለን" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 10:56
t.me/sputnik_ethiopia/8875
13
2
862
"የኢትዮጵያን ቅርሶች መሸጥ፤ የኢትዮጵያን ማንነት እንደ መሸጥ ይቆጠራል"

"ንብረቶቹ ለጨረታ ሲቀርቡ በቤተሰብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያዊም ተጎድተናል" ሲሉ የራስ ደስታ ዳምጠው የልጅ ልጅ ወ/ሮ የሺመቤት ካሳ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በጣሊያን ፋሺዝም ዘመን የኢትዮጵያ ትግል ምልክቶች የሆኑት የራስ ደስታ ሰይፍ እና ካባ—በቅርቡ በጣሊያን ጨረታ ላይ መቅረባቸው የሚታወስ ነው።

😡 ቁጣው የግል ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ ነው።

"እነዚህ ቅርሶች…የኢትዮጵያ ማንነት አካል ናቸው። …ሰዎች በዚህ ጀግና ሰው ስምና ንብረቶች ትርፍ ለማግኘት ሲሞክሩ በጣም እናዝናለን" ብለዋል።

የእነዚህ ቅርሶች ሽያጭ የባህል ቅኝ አገዛዝ ነው። ታሪክን ገፎ ለትርፍ መሸጥ። የምዕራባውያን ትርክቶች ደግሞ የአፍሪካን ደማቅ አሻራ ችላ ማለታቸውን ቀጥለዋል ሲሉም አክለዋል።

🌍 ወ/ሮ የሺመቤት ንብረቶቹን ለማስመለስ ዓለም አቀፍ ትብብር በተለይም እንደ ብሪክስ፣ ዩኔስኮ እና በመሳሰሉት ተቋማት በኩል እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

"ከእነዚህ ቡድኖች አባል ሀገራት የሚገኝ ጫና…እጅግ ጠቃሚ ነው" ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/26/2025, 09:39
t.me/sputnik_ethiopia/8874
16
1
1.6 k
#viral | የታይላንድ ፖሊስ አነስተኛ አውሮፕላን ባህር ውስጥ ተከስክሶ በውስጡ የነበሩ ተሳፋሪዎች በሙሉ ሕይወታቸው አለፈ

ስድስት መኮንኖችን ጭኖ ለፓራሹት ልምምድ የወጣው አውሮፕላን በታይላንድ ባህረ ሰላጤ ውስጥ በአሳዛኝ ሁኔታ ተከስክሷል።

የአደጋውን መንስዔ ለማወቅ ባለሥልጣናት ምርመራ ጀምረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 19:45
t.me/sputnik_ethiopia/8873
15
1
1.6 k
🇪🇹🇧🇷✈️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከብራዚሉ ኤምብራየር ኩባንያ አውሮፕላን ለመግዛት ጥናት እያደረገ እንደሆነ ገለፀ

አዲስ አበባ በተካሄደው የኢትዮጵያ አቪየሽን ፎረም ላይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገለጻ ያደረጉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፤ ለሀገር ወስጥ በረራ ብዙ ተሳፋሪ የሚይዙ አውሮፕላኖችን የመግዛት እቅድ እንዳለ ጠቁመዋል።

🗣 "የሀገር ውስጥ በረራ ፍላጎት ጨምሯል። ትላልቅ አውሮፕላኖች ያስፈልጉናል። በአሁኑ ጊዜ ሁለት የአውሮፕላን ሞዴሎችን እየገመገምን ነው። ከእነዚህ አንዱ ሞዴል ኢምብራየር ኤ2 አውሮፕላን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው መንግሥቴ በበኩላቸው ኢምብራየር በኢትዮጵያ ሥራ እንዲጀምር ፍላጎት እንዳለ ገልጸዋል። አክለውም ይህ አህጉሪቱንም የሚጠቅም ነው ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 19:21
t.me/sputnik_ethiopia/8872
6
1
1.5 k
❗️የፑቲን እና ዊትኮፍ ውይይት በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ቀጥተኛ ንግግሮች ዳግም ማስጀመር ላይ ያተኮረ እንደነበረ የክሬምሊን ረዳት ኡሻኮቭ ገለፁ

ዛሬ የተደረገው ውይይት በዩክሬን ብቻ ሳይሆን በሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም ለመያዝ አስችሏል ብለዋል።

ውይይቱ ለሦስት ሰዓታት የዘለቀና ገንቢና ጠቃሚ ነበር ተብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 18:49
t.me/sputnik_ethiopia/8871
11
1
1.5 k
የድል መሳሪያዎች - በዘይት እና በባሩድ የተነከረ። በእሳት እና በብረት የተወለደ - "ሁሉም ነገር ለጦር ግንባር! ሁሉም ነገር ለድል!" መሬት፣ አየር፣ መድፍ - ብረት ብቻ ሳይሆን የታላቁ ጀብድ ጸጥ ያሉ ምስክሮች ናቸው!

ስፑትኒክ የጦርነቱን ጀርባ የሰበሩ የድል ጦር መሣሪያዎችን በ3D ሞዴል ያቀርብሎታል።

▶️ በዚህ ከፍል የአየር ወለድ መከላከያው፦MIG-3

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 18:07
t.me/sputnik_ethiopia/8870
7
1
1.4 k
❗️በስፑትኒክ ዘጋቢ መረጃ መሰረት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ዊትኮፍን የያዘው ተሽከርካሪ ከክሬምሊን ወጥቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 17:52
t.me/sputnik_ethiopia/8869
2
1.4 k
ለጀርመን ናዚነት የአሜሪካ መነሻ፣ ክፍል 8 

በአሜሪካ ‘ኡንታሜንች’ የተሰኘውን ብያኔ ማን ፈጠረው ፣ ናዚዎች ለምን እና እንዴት ተገበሩት?

ከናዚ ርዕዮተ ዓለም መሠረቶች አንዱ አርያንስ ከሰው በላይ ናቸው የሚለው እምነት ነው። ‘‘ኡንታሜንች’’ ወይም ‘‘ ከሰዉ በታች’’ የሚል ብያኔንም፣  ሙሉ ሰዎች አይደሉም ብለው የሚያስቧቸውን እንደ አይሁዶች፣ ሮማንያውያን እና የስላቪክ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ለመግለፅ ይጠቀሙ ነበር፡፡

ሆኖም፣ የዚህ ቃል አመጣጥ እና የዘር ተዋረድ ጽንሰ-ሀሳብ ለመጀመሪያ የተፈጠረው በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ነው።

በዚህ ልዩ የስፑትኒክ ተከታታይ ስምንተኛው ቪዲዮ ላይም  የናዚዝም ታሪክ ጸሐፊ እና “የዋር ኦፍ አንሂሌሽን” ደራሲ ኢጎር ያኮቭሌቭ ፣ በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ማን እንደፈጠረው እና ማን ታዋቂ እንዲሆን እንዳደረገ ገልፀዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 17:46
t.me/sputnik_ethiopia/8868
4
1
1.5 k
🇪🇹🇨🇳 ሁለት የቻይና አየር መንገዶች በቅርቡ በኢትዮጵያ የበረራ አገልግሎት ለመጀመር ማቀዳቸው ተሰማ

አፍሪካን ወርልድ እና ሀይናን የተባሉት እነዚህ አየር መንገዶች በያዝነው የፈረንጆቹ 2025 መጨረሻ አገልግሎቱን ለመጀመር አቅደዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው መንግሥቴ ከሁለቱ የበረራ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።

የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ከኢትዮጵያ እና ቻይና የትብብር መስኮች አንዱ መሆኑን ገልፀው፤ በሀገራቱ የአየር አገልግሎት ስምምነት መሠረት ባለሥልጣኑ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 17:05
t.me/sputnik_ethiopia/8867
7
1.5 k
🇪🇹 ከ47 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የኢትዮ ቴሌኮም ባለድርሻ ለመሆን አክሲዮን ገዙ

ከጥቅምት 6 ቀን እስከ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በተከናወነው የኩባንያው 10 በመቶ አክሲዮን ሺያጭ 3.2 ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር ማግኘቱን አስታውቋል፡፡

የተሸጡ አክሲዮኖች ድልድል በካፒታል ገበያ ባለስልጣን የማጽደቅ ሂደት ከተከናወነ በኋላ ውጤቱን በይፋ የሚያሳውቅ መሆኑን ኩባንያው ገልጿል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 16:24
t.me/sputnik_ethiopia/8866
8
1
1.4 k
🇪🇹🇲🇦 ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ መተባበር በሚችሉበት መንገድ ዙሪያ መከሩ

ከሮያል ሞሮኮ የጦር ኃይሎች የተውጣጣ ከፍተኛ የጦር ልዑክ በዛሬው እለት የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል፡፡

ልዑኩ ኢንስቲትዩቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በተለያዩ ዘርፎች በማዋሃድ ላከናወነው ምሳሌያዊ ሥራ አድናቆቱን ገልጿል።

ሞሮኮ እና ኢትዮጵያ በዘርፉ ትብብር ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውንም ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 16:09
t.me/sputnik_ethiopia/8865
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8864
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8863
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8861
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8862
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8860
8
1.3 k
🇪🇹🇷🇺 የሩሲያ-አፍሪካ ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ዓድዋ ሙዚየምንና ብሔራዊ ቤተ-መንግሥትን ጎበኘ

ቡድኑ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የጋራ ምላሽ ልምምድ እና አውደ-ጥናት ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 15:38
t.me/sputnik_ethiopia/8859
10
3
1.4 k
"ወደ ኔቶ መቀላቀል ይችላሉ ብዬ አላስብም"፦ ትራምፕ ከታይም መፅሄት ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ስለ ዩክሬን የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

◾️ክሬሚያ በዩክሬን የሰላም ስምምነት መሠረት "የሩሲያ ግዛት ሆና ትቀጥላለች"፤ ዘለንስኪም ይህን ይረዳል፡፡

◾️የግጭቱ መነሻ የዩክሬን የኔቶ አባልነት ውይይት በመሆኑ ኪዬቭ ግጭቱን በማስነሳት ተጠያቂ ናት፡፡

◾️በዩክሬን ዙሪያ የሚደረገው ድርድር በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው፤ ስምምነቱ "በጣም ተቃርቧል"፡፡

◾️በፕሬዝዳትነታቸው ጊዜ በዩክሬን ሰላም እንደሚመጣ ያምናሉ፡፡

◾️ግጭቱን በአንድ ቀን ውስጥ ማቆም እችላለሁ የሚለው ንግግራቸው ማጋነን እና ምሳሌያዊ አነጋገር እንደሆነ አምነው፤ ግጭቱን ለማቆም ቃል ገብተዋል፡፡

◾️በዩክሬን ያለው ግጭት ለረጅም ጊዜ አይቀጥልም ብለዋል፡፡

◾️በሞስኮ እና በኪዬቭ መካከል ስምምነት ከተደረሰ አሜሪካ ከዩክሬን እና ሩሲያ ጋር የንግድ ግንኙነት ማድረግ የምትችልበትን ሁኔታ ትገመግማለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 15:23
t.me/sputnik_ethiopia/8858
8
2
1.4 k
❗️እንዴት ኖት፣ ክቡር ፕሬዝዳንት?

ክሬምሊን የፑቲን እና የዊትኮፍ ውይይት መጀመሩን የሚያሳይ ቪዲዮ ለቀቀ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 14:52
t.me/sputnik_ethiopia/8857
7
1
1.5 k
❗️ ፑቲን የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍን በክሬምሊን መቀበላቸውን የፑቲን ቃል አቀባይ ገለፁ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 14:30
t.me/sputnik_ethiopia/8856
3
1.5 k
ደቡብ አፍሪካ ለአሜሪካ የንግድ እቅድ ሃሳብ እያዘጋጀች ነው ሲሉ የሀገሪቱ የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ዩናይትድ ስቴትስ በደቡብ አፍሪካ ምርቶች ላይ የቀረጥ ጭማሪ ማድረጓን ብታስታውቅም በአሁኑ ስዓት ባለበት 10 በመቶ መቀጠሉን ኤኞክ ጎዶንግዋናሀ  ዋሽንግተን በተካሄደው የአይኤምኤፍ እና የዓለም ባንክ ስብሰባ ላይ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ዶናልድ ትራምፕ ሚያዚያ 1 ከ75 በላይ በሆኑ ሀገራት ላይ ከ10 በመቶ የሚጀምር ጠረፍ ለ90 ቀናት እንደጣሉ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 14:02
t.me/sputnik_ethiopia/8855
6
1.5 k
🇪🇹 የኢትዮጵያ አምራች ኢዱስትሪዎች የሚለቁትን የሙቀት ዓማቂ ጋዝ ልቀት ለመቀነስ ያለመ ስምምነት ተፈረመ

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፓን አፍሪካ ግሪን ኢነረጂ ጋር በትብብር ለመሥራት መግባባት ላይ ደርሷል።

ድርጅቱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎችን የድንጋይ ከሰል የሚተካ ግብዓት ከፕሮሶፒስ ጁሊፍሎራ አረም ባዮ ማስ እንደሚያመረት ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የድንጋይ ከሰል ከሚጠቀሙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች አንድ ቶን ሲሚንቶ በማምረት ሂደት ከሚለቀቀው የሙቀት ዓማቂ ጋዝ ልቀት ውስጥ 0.03 ቶን የሙቀት ዓማቂ ጋዝ ልቀት ለመቀነስ ዓላማ አለው።

የምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማድረግ እና የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም መገንባት ሌላው የስምምነቱ ትኩረት እንደሆነ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 13:39
t.me/sputnik_ethiopia/8854
25
1.5 k
🇪🇹 የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በቀጣዩ የበጀት ዓመት ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንደሚል የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ አስታወቀ

የባንኩ አስተዳዳሪ ማሞ ምሕረቱ ትናንት በዋሽንግተን በተካሄደው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና ዓለም ባንክ ስብሰባ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የዋጋ ግሽበቱ በመጋቢት ወር 13 በመቶ መደረሱን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ በእጥፍ ያድጋል ብለው እንደሚጠብቁ እና ከውጭ የሚላክ ገንዘብ በትንሹ በ25 በመቶ ሊጨምር እንደሚችልም ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

በተጨማሪም የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ከፍተኛ እድገት ማሳያቱን አስታውቀዋል፡፡

🗣 "ከማሻሻያው በኋላ የውጭ ምንዛሪ ክምችታችን በሦስት እጥፍ ጨምሯል። በባንክ ሥርዓቱ ያለው ክምችት በእጥፍ ጨምሯል፡፡ በኢኮኖሚው የካፒታል ፍሰት ላይ ግልፅ እድገት እና ጥንካሬ ይታያል" ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 12:37
t.me/sputnik_ethiopia/8853
04/25/2025, 11:47
t.me/sputnik_ethiopia/8850
04/25/2025, 11:47
t.me/sputnik_ethiopia/8851
04/25/2025, 11:47
t.me/sputnik_ethiopia/8852
13
1.4 k
🇪🇹 ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶቿን ለብሪክስ ሀገራት ማስተዋወቅ አለባት ሲሉ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ተናገሩ

ኖሴባ ናንሲ ሎሲ ይህን ያሉት የባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክን ከጎበኙ በኋላ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ነው፡፡

አምባሳደሯ የደቡብ አፍሪካ እና የኢትዮጵያ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግኑኝነት በቱሪዝም ዘርፉም እንደሚታይ ተናግረዋል፡፡

🗣 አክለውም "ሁለቱ ሀገራት የብሪክስ አባል እንደመሆናቸው፤ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቦታዎችን ለብሪክስ አባላትም ማስተዋወቃቸው ጠቃሚ ነው" ብለዋል፡፡

የቱሪዝም ሚንስቴር ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮች ባዘጋጀው የጉብኝት መርሃ ግብር ከ20 በላይ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል።

የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በ2016 ዓ.ም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በዓለም አቀፍ ቅርስነት መመዝገቡ የሚታወስ ነው፡፡


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 11:47
t.me/sputnik_ethiopia/8849
11
1.5 k
"አፍሪካ ከሩሲያ ጋር ባላት አጋርነት ላይ በማተኮር እያንሰራራች ነው"

በዓለም የወጣቶች ፌስቲቫል የካሜሩን ልዑካን ቡድን ፕሬዝዳንት የሆኑት ኒኮላስ ቢቦም አፍሪካ በፍጥነት ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም በተለይም ከሞስኮ ጋር የልማት ትብብር ዕድሎችን እየፈለገች እንደሆነ ተናግሯል።

"አፍሪካ ዕድገትን እና ልማትን ለማምጣት የምትጥር አህጉር ናት፤ ለመርዳትና ለመደገፍ ለሚችሉ አጋሮች ሁሉ በሯን ክፍት እያደረገች ነው" ሲሉ ቢቦም በአራተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የወጣቶች መድረክ ላይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በተጨማሪም የወጣቶች ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ወጣት አፍሪካውያን የሚማሩበት፣ እውቀት የሚያገኙበት እና ሀገራቸውን የሚገነቡበት እና የሚያሳድጉበት መድረክ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 11:07
t.me/sputnik_ethiopia/8848
7
3
1.6 k
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከሲቢኤስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

▫️በዩክሬን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር የሚደረገው ግንኙነት ቀጥሏል፣

▫️ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ላይ ለመስማማት ዝግጁ ናት፤ ነገር ግን አንዳንድ ዝርዝር ጉዳዮች "መስተካከል" ያስፈልጋቸዋል፣

▫️የዩክሬን ግጭት መንስዔ መፈታት እንዳለበት የሚገነዘቡ ብቸኛው መሪ ትራምፕ ናቸው፣

▫️ትራምፕ ዩክሬንን የኔቶ አባል ለማድረግ መሞከር ስህተት እንደሆነ ይረዳሉ፣

▫️ትራምፕ የሰላም ሂደቱ በትክክለኛው መንገድ እየሄደ ነው ብለው ያምናሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 10:37
t.me/sputnik_ethiopia/8847
9
1.7 k
❗️ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ ናት፤ ሆኖም አንዳንድ "መስተካከል" ያለባቸው ጉዳዮች አሉ ሲሉ ላቭሮቭ ተናገሩ
 
"በርካታ ምልክቶች ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ እየተጓዝን መሆናችንን ያመለክታሉ። በመጀመሪያ ደረጃ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዓለም ላይ የዚህን ሁኔታ መሠረታዊ መንስዔ የመፍታት አስፈላጊነትን የተረዱ ብቸኛው መሪ ናቸው ሊባል ይችላል" ሲሉ የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ለሲቢኤስ ኒውስ ተናግረዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 09:28
t.me/sputnik_ethiopia/8846
2
1.9 k
04/25/2025, 06:29
t.me/sputnik_ethiopia/8845
17
2
1.9 k
🇪🇹✈️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የብሪክስ ሀገራትን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ እንደሚሠራ ገለፀ

ይህ የተገለፀው በዛሬው እለት በተከፈተው የመጀመሪያው የኢትዮጲያ የአቪዬሽን ፎረም ላይ ነው።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስብሰባ በዘርፉ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ምክክር፣ የልምድ ልውውጥ እና ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሄዎች እንደሚፈለጉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተናግረዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አየር መንገዱ የብሪክስ ሀገራትን የአየር ትራንስፖርት በማሳደግ ረገድ የበኩልን ሚና የሚጫወትበትን መንገድ እያጤነ እንደሆነ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

"በብሪክስ ማሕበረሰብ ውስጥ ንግድ ለመጨመር እንቅስቃሴ አለ። በብሪክስ ህብረት ኩባንያዎች ሊተባበሩባቸው ከሚችሉባቸው መስኮች ውስጥ አንዱ የአየር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በብሪክስ ሀገራት መካከል የአቪዬሽን ኢንዱስትሪውን በማሳደግ ረገድ ሊጫወተው የሚችለውን ሚና በተመለከተ ጥናት እያካሄደ ነው። ይህንን ከሌሎች የብሪክስ አባላት ጋር በመሆን መዳሰሳችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/25/2025, 06:29
t.me/sputnik_ethiopia/8844
7
2.0 k
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን አሁን ኤክስ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ
https://x.com/sputnik_ethio

ይቀላቀሉ፣ አስተያየት ይስጡ፣ ልጥፎችን ያጋሩ። እንኳን በደህና መጣችሁ!
04/24/2025, 23:37
t.me/sputnik_ethiopia/8843
1
1.1 k
🇪🇹✈️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የብሪክስ ሀገራትን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ እንደሚሠራ ገለፀ

ይህ የተገለፀው በዛሬው እለት በተከፈተው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ፎረም ላይ ነው።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስብሰባ በዘርፉ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ምክክር፣ የልምድ ልውውጥ እና ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሄዎች እንደሚፈለጉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተናግረዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አየር መንገዱ የብሪክስ ሀገራትን የአየር ትራንስፖርት በማሳደግ ረገድ የበኩልን ሚና የሚጫወትበትን መንገድ እያጤነ እንደሆነ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

"በብሪክስ ማሕበረሰብ ውስጥ ንግድ ለመጨመር እንቅስቃሴ አለ። በብሪክስ ህብረት ኩባንያዎች ሊተባበሩባቸው ከሚችሉባቸው መስኮች ውስጥ አንዱ የአየር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በብሪክስ ሀገራት መካከል የአቪዬሽን ኢንዱስትሪውን በማሳደግ ረገድ ሊጫወተው የሚችለውን ሚና በተመለከተ ጥናት እያካሄደ ነው። ይህንን ከሌሎች የብሪክስ አባላት ጋር በመሆን መዳሰሳችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 21:09
t.me/sputnik_ethiopia/8842
1
1.0 k
04/24/2025, 21:09
t.me/sputnik_ethiopia/8841
13
1
985
04/24/2025, 21:09
t.me/sputnik_ethiopia/8840
21
1
2.0 k
ሩሲያ የዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤትን የሚተካ ተቋም በብሪክስ ማዕቀፍ ውስጥ ማቋቋምን ላጤንበት እችላለው አለች

የሩሲያ የፀጥታው ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ቀደም ሲል ብሪክስ "በማይመለስ መልኩ ጉድለት ያለበት" እና "ውጤታማ አይደለም" ላሉት የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ምትክ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው ነበር።

🗣 የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለሜድቬዴቭ ሃሳብ ምላሽ ሲሰጡ "ተነሳሽነቱ በእርግጥ ተሰርቷል እናም በብሪክስ አባል ሀገራት ማዕቀፍ ውስጥ የዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አማራጭ ስለማቋቋም ከአጋሮቻችን ጋር ውይይት ማድረጋችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 20:27
t.me/sputnik_ethiopia/8839
04/24/2025, 19:52
t.me/sputnik_ethiopia/8838
12
1.8 k
#viral |🇹🇷 በቱርክ የመሬት መንቀጥቀጥ ጀግና ነርሶች ህጻናትን ሲያድኑ የሚያሳይ ቪዲዮ

የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ረቡዕ ዕለት በኢስታንቡል በደረሰው የ6.2 ሬክተር ስኬል የመሬት መንቀጥቀጥ የተጎዱ ስዎች ቁጥር 236 ደርሷል ብሏል።

ለጉዳቶቹ ዋነኛ መንስኤ ድንጋጤ እና ሰዎች ከፎቆች ላይ መዝለላቸው እንደሆነ ተገልጿል። (ቪዲዮ 2☝🏽)

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


✅ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 19:52
t.me/sputnik_ethiopia/8837
14
3
1.7 k
ዩክሬን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ ነች ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ራማፎሳ ተናገሩ

"[..] ዘለንስኪ እራሳቸው እንደሚናገሩት ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለመወያየት እና ለመደራደር እንዲሁም ሁሉን አቀፍ እና  ቅድመ ሁኔታ የሌለው የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ነግረውኛል" ብለዋል።

በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ሰላማዊ መፍትሄ ለማረጋገጥ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ክሬምሊን "የሞስኮን ጥቅም ግምት ውስጥ ማስገባት ቀውሱን ለመፍታት ቅድመ ሁኔታ ነው" ሲል ቀደም ብሎ ገልጿል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


✅ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 19:51
t.me/sputnik_ethiopia/8836
18
1.7 k
የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዝዳንት ከግቡ 'ተሰናክሏል' ላሉት ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ብሪክስ አማራጭ ሊሆን እንደሚችል ጠቆሙ

ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ 'የጠፉ ቅዠቶች' በሚለው ጽሑፋቸው ፍርድ ቤቱ ምዕራቡን ዓለም እንደሚያስቀድም እና የኔቶን ወንጀሎች ችላ እያለ ደካማ ሀገራትን እንደሚያሳድድ ተናግረዋል።

🗣 በአሁኑ ጊዜ የሩሲያ የደህንነት ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት ሜድቬዴቭ "ፍርድ ቤቱ የሚኮንነው ወይም ይቅር የሚለው የምዕራቡ ዓለም ጥቅም ላይና በድርብ መመዘኛዎች ተመስርቶ ነው " በማለት አሜሪካ ፍርድ ቤቱን በንቀት እንደምትመለከት አስታውሰዋል።

🌐 አክለውም የታቀደው አዲሱ የፍርድ አካል ዓለም አቀፍ ሕግ ላይ በመመሥረት የዘር ማጥፋት፣ የጦር ወንጀል እና ሽብርተኝነት ላይ ያተኩራል ያሉት የቀድሞው ፕሬዝዳንት፤ የሀገር መሪዎችን ያለመከሰስ መብት እና ጣልቃ አለመግባትን አፅንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 19:01
t.me/sputnik_ethiopia/8835
8
1
1.8 k
#viral | 🐻 የብስኩት አምሮቱን የተወጣው የድብ ቤተሰብ

📍በደቡባዊ ቼክ ሪፐብሊክ ከተማ ጂህላቫ አቅራቢያ ቱሪስቶች ናቸው ለድቦቹ ብስኩቱን የቸሩት

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 18:14
t.me/sputnik_ethiopia/8834
22
1.9 k
🇪🇹 ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ከ12 ሚሊየን ኩንታል በላይ ሲሚንቶ ለገበያ አቀረበ

ፋብሪካው ምርቱን ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ እንዳቀረበ አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ዓመት መጀመሪያ የመረቁት ይሄ ፋብሪካ ከ1 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

የፋብሪካው ምርት ገበያውን ከማረጋጋት ባሻገር በኮንስትራክሽን ዘርፉ ላይ መነቃቃት ፈጥሯል ተብሏል።

በኢትዮጵያው ኢስት አፍሪካ ሆልዲንግና በቻይናው ዌስት ኢንተርናሽናል ሆልዲንግ በሽርክና የተገነባ ሲሆን በቀን አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ የማምረት አቅም አለው።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 17:29
t.me/sputnik_ethiopia/8833
12
2
1.8 k
🇪🇹 የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በብዛት በመሰመራት ቀዳሚ እንደሆኑ ተገለጸ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከተሳቡ የውጭ ኢንቨስትመንቶች ውስጥ ኬሚካልና ኮንስትራክሽን ከፍተኛውን ድርሻ እንድሚይዝ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም ከ12 ሃገራት የመጡ የውጭ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን እያፈሰሱ እንደሆነ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ ሀገራቱ ከታች የተዘረዘሩት ናቸው፦

🇨🇳ቻይና - 114

🇮🇳ህንድ -7

🇦🇪ዩናይትድ አረብ ኤምሬቶች - 4

🇨🇦ካናዳ - 3

🇳🇱ኔዘርላንድ - 3

🇺🇸አሜሪካ - 2

🇹🇷ቱርክ - 2

🇸🇦ሳዑዲ አረቢያ -1

🇧🇩ባንግላዲሽ -1

🇸🇩ሱዳን -1

🇳🇿ኒውዝላንድ -1

🇲🇺ሞርሸስ -1

በስርጭት ደረጃ ሲታይ በአዲስ አበባ 76፣ በኦሮማያ 48፣ በአማራ 13፣ በትግራይ 4፣ በሲዳማ 3 እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያና አፋር እያንዳንዳቸው አንድ የውጭ ባለሀብት ወደ ሥራ አስገብተዋል።

ወደ ማምረት ከተሸጋገሩት ውስጥ የምግብና መጠጥ፣ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ የጨርቃጨርቅና አልባሳት እና የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ዘርፍ እንደ ቅደም ተከተላቸው ደረጃ መያዝቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አሳይቷል፡፡


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 17:07
t.me/sputnik_ethiopia/8832
13
1.8 k
🇪🇹 በኢትዮጵያ በ72 ከተሞች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማሻሻያ በቅርቡ ተግባራዊ ይሆናል ተባለ

አስራ አንድ ክልሎችን የሚያካትተው ይሄ ፕሮጀክት በሁለት ምዕራፎች የሚተገበር ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ 34 ሁለተኛው ደግሞ ተጨማሪ 38 ከተሞችን ይሸፍናል።

ማሻሻያው የሀገሪቱ የኃይል ስርዓቶችን ዘመናዊ ማድረግ እና በአካባቢ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለመደገፍ የታሰበው ስትራቴጂ አካል ነው ተብሏል።

የፕሮጀክት ኃይል አቅርቦት ጥራትና አስተማማኝነትን ማሻሻል፣ የትራንስፎርመር አቅምን ማሳደግ፣ የኃይል ኪሳራን መቀነስ እና የቮልቴጅ መለዋወጥን ማረጋጋት የእቅዱ ትኩረት እንደሆነም ተገልጿል።

በዚህም 6 ሺህ 183 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው የመካከለኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ መስመሮች ማሻሻያ እንደሚደረግባቸው የተገለጸ ሲሆን የ5 ሺህ 569 ማከፋፈያ ትራንስፎርመሮችን አቅም ያሳድጋል ተብሏል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 16:24
t.me/sputnik_ethiopia/8831
12
1
1.6 k
ከአዲስ አበባ የሚመነጩ ቆሻሻዎች ወደ ታዳሽ ኃይል ሊቀየሩ ነው

ከአዲስ አበባ መንጭተው ረጲ አካባቢ የሚጣሉ ቆሻሻዎችን ወደ ኢኮ ፓርክነት የሚቀይር እና የኃይል አማራጭን በማስፋት ተጨማሪ ገቢ ያስገኛል የተባለ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈርሟል፡፡

ስምምነቱ የተፈረመው በቻይና ሻንዥን ኢነርጂ ግሩፕ፣ የቻይና ብሔራዊ ኤሌክትሪክ ኢንጅነሪንግ ድርጅት እና በጀርመኑ ኮቬናንት ኢንጅነሪንግ ድርጅት መካከል ነው፡፡

ፕሮጀክቱ ከተማዋን ውብ እና ፅዱ እንዲሁም ስማርት ሲቲ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን የሚያግዝ ነው መባሉን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 16:05
t.me/sputnik_ethiopia/8830
12
1.7 k
የድል መሳሪያዎች - በዘይት እና በባሩድ የተነከረ። በእሳት እና በብረት የተወለደ - "ሁሉም ነገር ለጦር ግንባር! ሁሉም ነገር ለድል!" መሬት፣ አየር፣ መድፍ - ብረት ብቻ ሳይሆን የታላቁ ጀብድ ጸጥ ያሉ ምስክሮች ናቸው!

ስፑትኒክ የጦርነቱን ጀርባ የሰበሩ የድል ጦር መሣሪያዎችን በ3D ሞዴል ያቀርብሎታል።

▶️ በዚህ ከፍል ብረት ለበስ የጠላት ጦር መሣሪያ አውዳሚው፦ISU-152


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 16:02
t.me/sputnik_ethiopia/8829
1
1.9 k
04/24/2025, 15:33
t.me/sputnik_ethiopia/8827
1
1.8 k
04/24/2025, 15:33
t.me/sputnik_ethiopia/8828
1
1.7 k
04/24/2025, 15:33
t.me/sputnik_ethiopia/8826
7
1
1.5 k
መረጃ ላይ "ፍትሃዊነትን" ማምጣት፦ በኢትዮጵያ የተካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ የመገናኛ ብዙሃን መድረክ

ዝግጅቱ "ሩሲያ-አፍሪካ የወዳጅነትና የትብብር መንገድ" በሚል ርዕስ ሚያዝያ 14 እና 15 በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

👉በውይይቱ አፍሪካ ጋዜጠኞች ያካበቱትን ልምድ ለስፑትኒክ አፍሪካ አጋርተዋል።

🗣 "ምዕራባውያን ለአፍሪካ የተለየ ዓይነት ትርክት ለመስጠት ባደረጉት ሆን ተብሎ የተደረገ ጥረት ምክንያት በአፍሪካ እና በዓለም ዙሪያ ያለው የመረጃ ፍሰት በተወሰነ መልኩ የተመጣጠነ መረጃ እጥረት አለበት። ሩሲያ አሁን በአፍሪካ ውስጥ ያለውን የመረጃ ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገች ነው።"
- ፍሬድ ኩኩ ስሚዝ፣ በጋና የጆይ ኒውስ/ጆይ ኤፍ ኤም አርታኢ

🗣 "በዚህ አይነት መድረኮች መሳተፋችን እንደ አፍሪካውያን ጋዜጠኞች እያገኘናቸው ሰላሉ መረጃዎች እንድንገነዝብ ያደርጋል። በተጨማሪም ከአዲሱ ቅኝ አገዛዝ ጋር ተመሳሳይነት ካለው የሚዲያ ሽፋን እንላቀቃልን።"
- ኢማህ ንኩቤ፣ የደቡብ አፍሪካ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የመልቲሚዲያ አርታኢ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 15:33
t.me/sputnik_ethiopia/8825
8
1.9 k
❗️የሩሲያ እና አሜሪካ የስለላ ተቋማት ኃላፊዎች "ገንቢ" ውይይት አካሄዱ

የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት ኃላፊ ሰርጌ ናሪሽኪን ከሲአይኤ ዋና ዳይሬክተር ጆን ራትክሊፍ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።

ናሪሽኪን ውይይቱን "በጣም ገንቢ" ሲሉ ለሩሲያ ሚዲያ የገለፁ ሲሆን ከሲአይኤ ዳይሬክተር ጋር በአካል ይገናኙ ይሆን ተጠይቀው ወድቅ ሳያደርጉት ቀርተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 14:33
t.me/sputnik_ethiopia/8824
6
5
1.8 k
አውሮፓ፤ ናዚዝም ድል ቢያደርግ ኖሮ

በሰው ሰራሽ አስተውሎት እወን የሆነ አማራጭ ታሪክ፦ ክፍል 1

ከታሪክ ክስተቶች ከሚነሱት አማራጭ መላምቶች አንዱ ሂትለር ድል አድርጎ ቢሆን ኖሮ የሚለው ነው። ሶቪየቶች የናዚ ጀርመንን ግስጋሴ ባያቆሙ ኖሮ ምን ይፈጠር ነበር? ስፑትኒክ በሂትለር እቅድ "መጪው ግዜ" ምን ሊሆን እንደሚችል በጋዜጠኞች የጽሑፍ ማህደር ሰነዶች ተመስርቶ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በተቀነባበረ ቪዲዮ ተከታታይ ፕሮጀክት ያቀርብሎታል!


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 14:15
t.me/sputnik_ethiopia/8823
2
1.9 k
04/24/2025, 13:23
t.me/sputnik_ethiopia/8822
2
2.0 k
04/24/2025, 13:23
t.me/sputnik_ethiopia/8821
2
1.9 k
04/24/2025, 13:23
t.me/sputnik_ethiopia/8820
7
2
1.7 k
#viral | 🌋በሩሲያ ካምቻትካ ክልል የሚገኙ መንደሮች ቤዚምያኒ እሳተ ገሞራ በፈጠረው ፍንዳታ በአመድ ተሸፈኑ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 13:22
t.me/sputnik_ethiopia/8819
9
1
1.9 k
ትራምፕ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝታቸው በኋላ ከፑቲን ጋር ለመገናኘት አቅደዋል ተባለ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከግንቦት 5 እስከ 8 ወደ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ይጓዛሉ።

🗣 "ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ እንገናኛለን (ከፑቲን ጋር) ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ የሩሲያ እና የአሜሪካ መሪዎች ግኑኝነት ፍሬያማ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ እና ዝግጅቶች ከውዲሁ እየተደረጉ እንደሆነ ረቡዕ ዕለት አስታውቀዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 12:00
t.me/sputnik_ethiopia/8818
15
3
1.8 k
🇪🇹 🔌 ጊቤ ሶስት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከእቅዱ በላይ ኃይል ማመንጨቱ ተገለፀ

በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4 ሺ 725 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ፤ 5 ሺ 436 ጊጋ ዋት ኃይል ማምረት ተችሏል።

ይህም ከእቅዱ የ15.4 በመቶ ብልጫ እንዳለው የኃይል ማመንጫው የኦፕሬሽን ኃላፊ ደጀኔ ጉታ አስታውቀዋል፡፡

አፈፃፀሙ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189.65 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3.61 በመቶ ብልጫ አለው።

የጊቤ 3 ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ18 ማመንጫ ጣቢያዎች ከተመረተው የ21 ሺ 299 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የ25.5 በመቶ ድርሻ በመያዝ የታላቁ ህዳሴ ግድብን ተከትሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 11:51
t.me/sputnik_ethiopia/8817
19
2
1.7 k
🇪🇹🌱 በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት የተተከሉ ችግኞች 85 በመቶ የጽድቀት መጠን እንዳላቸው ተገለጸ

በመጪው ክረምት በክልሉ በ207 ሺህ ሄክታር ላይ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው።

ችግኞቹ የሚተከሉት በተጎዱ መሬቶች ላይ እንደሆነ የክልሉ የግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ የክልሉን የደን ሽፋን አሁን ካለበት 16.3 በመቶ ወደ 17.3 በመቶ ለማሳደግ ታሳቢ መደረጉ ተነግሯል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 11:20
t.me/sputnik_ethiopia/8816
10
3
1.7 k
ኪንሻሳ እና ኤም23 ወደ "እርቅ" መመለስ እንደሚፈልጉ አስታወቁ

ይሕ የተገለጸው የኮንጎ መንግሥት እና የኮንጎ ወንዝ ጥምረት ሚያዝያ 15 ቀን በኳታር ካደረጉት ንግግር በኋላ በሰጡት የጋራ መግለጫ ነው።

በመግለጫቸው ሁለቱ ወገኖች "ግጭት ለማቆም ቁርጠኛ እንደሆኑ ያረጋገጡ" ሲሆን በድርድሩ ወቅት የተኩስ አቁሙን ለመቀጠልም ቃል ገብተዋል።

የጋራ መግለጫው የፍላጎት መግለጫ ወይም ወዲያው ተግባራዊ የሚደረግ ስምምነት እንደሆነ ግልጽ አይደለም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 11:05
t.me/sputnik_ethiopia/8815
2
1.6 k
04/24/2025, 10:51
t.me/sputnik_ethiopia/8814
8
2
1.7 k
የሩሲያ ግዙፍ የአልማዝ ኩባንያ የዚምባብዌን የኢንቨስትመንት ምህዳር አበረታች ሲል አወደሰ

የዚምባበዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ በዓለም ትልቁ የአልማዝ አምራች ከሆነው አልሮሳ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር በሀገሪቱ እምቅ የአልማዝ ኢንዱስትሪ አቅም ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

የአልሮሳ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፓቬል ማሪኒቼቭ መንግሥት የፈጠረው ምቹ እና አበረታች የኢንቨስትመንት ምህዳር ኩባንያው በዚምባብዌ እንዲሠማራ ፍላጎት እንዲኖረው ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 10:51
t.me/sputnik_ethiopia/8813
22
2
1.9 k
በአፍሪካ ለሩሲያ ጠላት የሆኑ ሀገራት የሉም ሲሉ የሩሲያ ባለስልጣን ተናገሩ

በሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ትብብር ቢሮ ኃላፊ ታትያና ዶቭጋለንኮ በሩሲያ እና አፍሪካ ግኑኝነት ዙሪያ ትኩረቱን ባደረገው ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር ሩሲያ እና አፍሪካ ተፈጥሯዊ አጋሮች ናቸው ብለዋል።

🗣 "የአፍሪካ አጋሮቻችን ሩሲያ የአዲሱ ባለብዙ ማዕከል ዓለም አንዷ መሪ እንደሆነች እንዲሁም ሉዓላዊነቷን መከላከል የምትችል እና ሌሎች ሀገራትንም በዚህ የመርዳት አቅም እንዳላት ማወቃቸው አስፈላጊ ነው" ብለዋል።

የአህጉሪቱ ሀገራት በሩሲያ ላይ በሚጣሉ ማዕቀቦች ላይ አልተሳተፉም ሲሉም ዲፕሎማቷ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

🗣 "አህጉሪቷ ቀስ በቀስ ራሱን የቻለች ዓለም አቀፍ ተዋናይ እየሆነች እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ተጽዕኖዋ እየጨመረ መጥቷል። ለአፍሪካ ችግሮች-የአፍሪካ መፍትሄዎች በሚለው ሀሳብ መሠረት አፍሪካ በተቋማት ላይ ትኩርት እያደረገች እና የአፍሪካ ሀገራትን ትብብር እያጠናከረች ነው" ሲሉ ዶቭጋለንኮ ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/24/2025, 10:35
t.me/sputnik_ethiopia/8812
17
1
1.9 k
🇷🇺🌍 ሩሲያ የአፍሪካን አቋም በማጠናከር ረገድ እገዛ እንደምታደርግ ላቭሮቭ ተናገሩ

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሞስኮ አፍሪካ በአዲሱ ዓለም አቀፍ ሥርዓት ውስጥ ነጻ ተዋናይ እንድትሆን ለመርዳት ቁርጠኛ ነች ብለዋል።

ላቭሮቭ ሩሲያ ለአፍሪካ ልማት ያላት ቁርጠኝነት

🟠 በሉዓላዊነት፣
🟠 በትምህርት፣
🟠 በላቁ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት ላይ ያተኮረ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ሩሲያ ለአፍሪካ የነጻነት ንቅናቄዎች ያደረገችውን ድጋፍ በማስታወስ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ታሪካዊ የወዳጅነት ትስስር አጉልተዋል።

👉 ላቭሮቭ አክለውም ሩሲያ እና የአፍሪካ አጋሮቿ አዲስ ቅኝ አገዛዝን ለመቃወም እና ገለልተኛ የኢኮኖሚ መፍትሄዎችን ለመመስረት በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን አንስተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 21:31
t.me/sputnik_ethiopia/8811
22
2
1.8 k
🇷🇺🌍 ሩሲያ የአፍሪካ ወዳጆቿን ወረርሽኝን የመዋጋት አቅም የሚያግዝ ሰፊ ፕሮግራም እንደጀመረች ፑቲን ገለፁ

ፑቲን በጤና አጠባበቅ እና ድንገተኛ ወረርሽኞች ምላሽ አሰጣጥ ላይ ባተኮረው የመጀመሪያው የሩሲያ-አፍሪካ ዓለም አቀፍ ልምምድ ላይ ባደረጉት ገለጻ የወረርሽኝ መከላከያ ፕሮግራሙ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፦

🟠 ከ150 በላይ የአፍሪካ ባለሙያዎችን እንዳሰለጠነ፣
🟠 በደርዘን በሚቆጠሩ አደገኛ ኢንፌክሽኖች ላይ የጋራ ምርምር ማካሄዱን እንዲሁም
🟠 ስድስት ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪዎችን ወደ አፍሪካ ሀገራት መላኩን ገልጸዋል።

እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ ኢትዮጵያ ውስጥ በሩሲያ፣ በ15 የአፍሪካ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል የሚደረገው የጋራ ልምምድ የእውቀት ልውውጥ እና ተላላፊ የበሽታ ወረርሽኞችን ለመከላከል ጠቃሚ መድረክ እንደሆነ አመልክተዋል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 19:45
t.me/sputnik_ethiopia/8810
16
3
2.0 k
ኢትዮጵያ፤ ፋሺስዝምን የመከተች እና ድል ያደረገች ሀገር፦ ክፍል 1

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢንዱስትሪ ምህንድስና ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው የታላቁን ድል 80ኛ ዓመት አስመልክቶ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ በዓድዋ እና በሁለተኛው ዓለም ጦርነት ያሳያችው የተጋድሎ ታሪክ የነጮችን የበላይነት በመቃወም ግንባር ቀደም እንድትሆን እንዳደረጋት ተናግረዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 19:11
t.me/sputnik_ethiopia/8809
4
1.9 k
04/23/2025, 18:46
t.me/sputnik_ethiopia/8808
15
4
1.6 k
🇪🇹🇷🇺 የሩሲያ ድጋፍ በጥቅሟ ላይ የተመረኮዘ አይደለም ሲሉ የሩሲያ የሸማቾች መብት እና የዜጎች ደህንነት ጥበቃ ኤጀንሲ ኃላፊ ተናገሩ

ኃላፊዋ ዶክተር አና ፖፖቫ ይሄን ያሉት የሩሲያ መንግሥት በዛሬው እለት ለኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ ያደረገውን ድጋፍ አስመልክቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት መግለጫ ነው። ኤጀንሲው ከተንቀሳቃሽ ላብራቶሪ ድጋፍ በተጨማሪ ለድንገተኛ ወረርሽኝ እና ለጤና ቀውስ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስምምነት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በዛሬው ዕለት ተፈራርሟል።

🗣 "ሩሲያ ከአፍሪካ አህጉር ጋር ወዳጃዊ፣ የመደጋገፍ እና በጋራ እርዳታ ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አላት። ይህ ደግሞ ድጋፍ በሚሰጠው አካል ጥቅም ላይ ከተመረኮዘው የሌሎች ሀገራት የእርዳታ አሰጣጥ ጋር ፍጹም የተለየ ነው" ብለዋል።

ኃላፊዋ አክለውም የሩሲያ የላብራቶሪ እርዳታ "ሀገራት የራሳቸውን ባዮሎጂ ነክ ስጋቶች መቋቋም አለባቸው" በሚለው መርህ ላይ የተመሠረተ እንደሆነ ተናግረዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 18:46
t.me/sputnik_ethiopia/8806
4
1.9 k
04/23/2025, 18:46
t.me/sputnik_ethiopia/8807
7
3
1.7 k
የደቡብ አፍሪካ የዋጋ ግሽበት በመጋቢት ወር በ2.7% ዝቅ ማለቱን መረጃ አመላከተ

የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት ግምት 2.9% የነበረ ሲሆን የሀገሪቱ ተጠባባቂ ባንክ 3% እንደሚሆን አስቀምጦ ነበር።

የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ በጀት እና የትራምፕ የንግድ ጦርነት ስጋቶችን በመጥቀስ ባለፈው ወር የወለድ ምጣኔውን ባለበት እንዲቆይ ወስኗል።

የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር ከነበረበት 0.9% በመጋቢት ወር በ0.4% ቀንሷል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 17:42
t.me/sputnik_ethiopia/8805
4
1
1.7 k
ደ ጉል፤ መጪውን ጊዜ ለመገንባት ታሪክን መጠበቅ፦ ክፍል 3

ለናዚነት መነሳት አውሮፓዉያን መንገድ ከፍተዋል፤ እናም ታሪክ ራሱን እንዳይደግም ልንከላከለው ይገባል ሲሉ ከስፑትኒክ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የቻርለስ ደ ጉል የልጅ ልጅ ተናገረዋል፡፡

“በዩክሬን ውስጥ ከፍተኛ ክፍፍሎሽ እንዳንፈጥር ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ አስባለሁ፡፡ ለናዚነት መልሶ ማንሰራራት ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ፤ ልንፈቅድ እንደማይገባ አምናለሁ፡፡”


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 17:15
t.me/sputnik_ethiopia/8804
5
1
1.8 k
🇨🇳🇰🇪 ቻይና እና ኬንያ በናይሮቢ አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕንፃ ለመገንባት ተስማሙ

ስምምነቱ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ወደ ቻይና የሥራ ጉብኝት ማደረግ ከመጀመራቸው ጋር ተያይዞ የተገለጸ ነው፡፡ ሩቶ ከቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በርካታ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ስምምነቶችን ይፈርማሉም ተብሎ ይጠበቃል።

የፕሮጀክቱ ዝርዝር ጉዳዮች፦

🟠 ግንባታው የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሥራዎች እየሰፉ በመምጣታቸው አስፈላጊ ሆኖ እንደተገኘ ተገልጿል፣

🟠 ቻይና የሁለቱን ሀገራት የ60 ዓመታት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን አስመልክቶ የተወሰነውን ገንዘብ ትሸፍናለች፣

🟠 የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት እየተካሄደ በመሆኑ የግንባታው ትክክለኛ ወጪ እስካሁን ይፋ አልተደረገም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 16:28
t.me/sputnik_ethiopia/8803
16
2
1.6 k
🇪🇹🌾 በኢትዮጵያ 1.6 ሚሊየን ሄክታር ላይ የተዘራ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት መሰብሰቡን ግብርና ሚኒስቴር ገለፀ

በዚህ ዓመት ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 172 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ እንደነበር የገለፁት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኢሳያስ ለማ፤ እስካሁን 3.5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡

አክለውም በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በስፋት ወደ ሥራ መገባቱንና 3.7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን 98 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

ኃላፊው የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርሶ አደሮች በመኸር፣ በበልግና በበጋ መስኖ ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ እየተሠራ መሆኑን ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 16:05
t.me/sputnik_ethiopia/8802
9
1.6 k
🇪🇹 በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ የሽብር ጥቃት በማክሸፍ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ

ስልጠናው በሶማሊያ በድጋፍ ሰጪነት ተሰማርተው ለሚገኙ የምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር አባላት እንደተሰጠ ተገልጿል። ከተባበሩት መንግሥታት የፈንጂ እርምጃ አገልግሎት ጋር በመተባበር የተሰጠው ስልጠና የንድፈ-ሀሳብ እና የተግባር ስልጠናን ያካተተ እንደነበር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

የሴክተር አራት ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ሹመት ጠለለው ሙያተኞቹ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት የተሰጣቸውን ተልእኮ በብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

🗣 "በየጊዜው ቴክኖሎጂዎች እየተሻሻሉ በመጡ ቁጥር ብዙ አማራጮች ይኖራሉ። ከግዳጅ ቀጣናው ጋር ተያይዞ አልሻባብ በዋናነት የሚጠቀምባቸውን ፈንጆች በመለየት እና ፍተሻዎችን በማድረግ ጉዳት ሳያደርሱ ማስወገድ ቀዳሚው ተግባር ነው" ሲሉ አሳስበዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 15:43
t.me/sputnik_ethiopia/8801
18
1.7 k
❗️ፑቲን በ2024 ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ድሮኖች ለሩሲያ ወታደሮች መላካቸውን ተናገሩ

እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ፦

🟠 ሩሲያ በ2024 የጦር መሳሪያ ምርቷን ከእጥፍ በላይ አሳድጋለች።

🟠 የሩሲያ ወታደሮች በ2024 ከ4 ሺህ በላይ ብረት ለበስ የጦር መሳሪያዎችን፣ 180 የውጊያ አውሮፕላኖችን እና ሄሊኮፕተሮችን ተረክበዋል።

አክለውም የተለያዩ ሀገራት ጦሮች እና የጦር መሣሪያ አምራቾች የሩሲያን በራስ አቅም ጦርነትን የማካሄድ ልምድ እያጠኑ ነው ብለዋል።

በዚህ ዓመት የሩሲያ ወታደራዊ-ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ከ2024 የበለጠ ትልቅ ግቦች እንዳሉትም መሪው አስታውቀዋል።

🗣 "ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን በማዳበር የወደፊት ግጭቶችን መተንበይ አለብን" ሲሉ ፑቲን ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ በወታደራዊ ኢንዱስትሪ ዙሪያ ያሉ ዓለም አቀፍ አዝማሚያዎችንም ግምት ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 14:55
t.me/sputnik_ethiopia/8800
3
1.6 k
❗️ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6.2 በተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተመታች

ምስሉ የሲኤንኤን ቱርክ ስቱዲዮ በመሬት መንቀጥቀጡ መናጡን መዝግቧል።

ተጨማሪ ምስል በዛሬው እለት በኢስታንቡል የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የፈጠረውን ድንጋጤ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
04/23/2025, 14:39
t.me/sputnik_ethiopia/8799
11
3
1.7 k
04/23/2025, 14:39
t.me/sputnik_ethiopia/8798
4
1.8 k
የስፑትኒክ ኢትዮጵያ መተግበሪያን አሁን በአንድሮይድ ማውረድ ይችላሉ።

ለአጠቃቀም በጣም ቀላል በሆነው መተግበሪያ የሚከተሉትን ያገኛሉ፦

🟠ቀላል አሰሳ
🟠ትኩስ የኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፍ ዜናዎች
🟠ልዩ ቃለመጠይቆች
🟠ምስላዊ መረጃዎች እና ቪዲዮዎች
🟠የወደዱትን በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ማጋራት

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡-

👉 APK ፋይል ሊንክ

👉 Galaxy Store

👉 GetApps

👉 AppGallery

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉@sputnik_ethiopia

#ad
04/23/2025, 14:35
t.me/sputnik_ethiopia/8797
Search results are limited to 100 messages.
Some features are available to premium users only.
You need to buy subscription to use them.
Filter
Message type
Similar message chronology:
Newest first
Similar messages not found
Messages
Find similar avatars
Channels 0
High
Title
Subscribers
No results match your search criteria