Your trial period has ended!
For full access to functionality, please pay for a premium subscription
FD
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://t.me/fdredefenseforc
Channel age
Created
Language
Amharic
0.42%
ER (week)
9.71%
ERR (week)

# ቁልፍ እሴቶች

1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣

2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣

3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣

Messages Statistics
Reposts and citations
Publication networks
Satellites
Contacts
History
Top categories
Main categories of messages will appear here.
Top mentions
The most frequent mentions of people, organizations and places appear here.
Found 3 888 results
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/22/2025, 10:48
t.me/fdredefenseforc/38876
የውትድርና ህይወት
የጥቁር አንበሳ - የጀግንነት ውርስ
ክፍል-1

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 06 ቀን 2017 ዓ.ም

የእናት ሀገር ፍቅር ውስጣቸው የሚንቀለቀል ደመ - ሞቃት ኢትዮጵያዊ ጀግኖች እዚህ ስፍራ የተገኙት ለአላማ ነው። ያሰባሰባቸው ብርቱ ጉዳይ አለ። ስፍራው ምስራቅ ወለጋ ነቀምት ከተማ አካባቢ ነዉ ። እንዴት እደፈራለሁ የሚል ኩሩ የኢትዮጵያዊነት ስብዕና የቀሰቀሳቸው ወጣቶች፤ ጦር የሰበቀባቸውን ጠላት ለመመከት ወኔ አልቸገራቸውም። ገድሎ ለመሞትም ይሁን ተዋግቶ ለማሸነፍ ፅናት አላጡም። ይልቁንም አደራጅቶ የሚያዋጋቸው መሪ ይፈልጉ ነበር።
እናም የወቅቱን ወጣቶች ክፍተት የሚሞሉ የገነት ጦር ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዙር ተመራቂ መኮንኖች በስፍራው ደረሱ። ሰኔ 19 ቀን 1928 ዓ.ም  "ጥቁር አንበሳ" በሚል ስያሜ የሀገር አለኝታና የህዝብ መከታ የሚሆን ማህበር አደራጅተው ፋሽስት ጣሊያንን በቁርጠኝነትና በጋራ ለመፋለም ቃለ መሃላ ፈፀሙ።

በውስጣቸው ከሀዲ ቢኖር እስከ ሞት ሊቀጡ ፣ ከመሀላቸው በአስገዳጅ ሁኔታ ጠላት እጅ የመውደቅ አደጋ ቢገጥም ቀድሞ ራስን ለማጥፋት ተስማሙ፣ ቃላቸውንም ላያጥፉ እርስ በእርሳቸዉ ተማማሉ ።
የሀገር ዳር ድንበር መደፈር ያንገበገባቸው ወጣቶች፣ የህዝብ ሉአላዊነት መነካት ያስቆጣቸው መኮንኖች በመሪና ተመሪ ተደራጅተው ወደ መሀል ሀገር የዘለቀውን የፋሽስት ጦር መውጫ መግቢያ አሳጡት። ሰኔ 20 ቀን 19 28 ዓ.ም ወለጋ ነቀምት ከተማ ልዩ ቦታው "በኬ ቦንያ " አካባቢ ነው።

የኢትዮጵያ አርበኞች ከፋሽስት ኢጣሊያ ጦር ጋር በወለጋ ተራራ እና ሸንተረሮች ላይ እየተፋለሙ ይገኛሉ። ጠላት ነቀምት ላይ ማዘዣውን በማድረግ በግንባር ለሚዋጋው ኃይሉ የውጊያ ድጋፍ ይሰጣል። የጥቁር አንበሳ ጀግና መኮንኖች የውጊያውን ኃይል ማዛባት እንዳለባቸው የገነት ጦር ትምህርት ቤት ስልጠናቸው አስታወሳቸው። በአጭር ጊዜ አቅደው ለትግበራ ተዘጋጁ። የጠላትን ስነ-ልቦና ለመስለብና ድል ለመቀዳጀት የጠላትን የስህበት ማዕከል ለዩ ። ማዘዣና አየር ኃይሉን ማጥቃት እንዳለባቸው ወሰኑ። በከፍተኛ የሰው ኃይልና በዘመናዊ መሳሪያ የሚጠበቀውን የጠላት ማዘዣና የአየር ኃይል ማጥቃት ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍል ተረድተውታል። ይሁን እንጂ "ምንም አይነት መስዋዕትነት ከሀገር በላይ አይሆንም " የጥቁር አንበሳዎች መርህ ነበር።

በዚሁ ቀን በልዩ ወታደራዊ ጥበብ እና በፍፁም የሀገር ፍቅር ወኔ የተሞሉት የጥቁር አንበሳ ጀግኖች ወደ አየር ኃይሉ በመገስገስ ድንገተኛ ጥቃት ሰነዘሩ። በእጃቸው የያዟቸውን ቦንቦች እየወረወሩ አውሮፕላኖችን በማጋየት ሊከላከል የሞከረውን የፍሽስት ጦር በጥይት እየቆሉ ቅፅበታዊ ማጥቃታቸውን ሰነዘሩ ። ድንገት ግቢውን የእሳት ረመጥ አድርገው ውስጡን በጭስ ሸፈኑት ። መግቢያ መውጫ ያጣውን ጠላት ከብበው አደባዩት። ጠላት በወረራ በያዛቸው ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንዲህ አይነት ውጊያ ገጥሞት የሚያውቅ አይመስልም።

ጠላት ይሆናል ያላለው ሲሆን ፣ ያላሳበው ሲፈፀም ወኔው ተሰልቦ የእውር ድንብሩን ብቻ ለመከላከል ሞከረ። የገጠመው ከኢትዮጵያዊ የጥቁር አንበሶች ነውና ሊሆንለት ግን አልቻለም።  ጀግኖቹ ኢላማቸውን እየለዩ ፣ የጠላትን ቁስ በማውደምና የሰው ኃይሉን በመደምሰስ በአጭር ሰአት ግዳጃቸውን መፈፀም ቻሉ። በስፍራው የነበሩ 3 አውሮፕላኖች ሙሉ በሙሉ ሲወድሙ ፓይለቶችን ጨምሮ 13 ከፍተኛ መኮንኖች እና የጠላት ወታደሮች ተገደሉ። በዚህ ልዩ ዘመቻ የጥቁር አንበሳ ተዋጊዎች የአሸናፊነት ስነ- ልቦና ሲገነባ የጠላት ሞራል በእጅጉ ሊላሽቅ ቻለ።

ዘመቻው ኢትዮጵያ ለጠላት የማትመች ፣መሬቷም ረመጥ መሆኗን ለፋሽስቶች መልዕክት ያስተላለፈ ክስተት ሆነ። የጥቁር አንበሳውን ጦር እየመሩ ይህንን ልዩ ዘመቻ በስኬት የፈፀሙት የገነት ጦር ትምህርት ቤት የመጀመሪያው ኮርስ ተመራቂ ሌተና ኮሎኔል በላይ ኃይለአብ ነበሩ።

የወቅቱ የገነት ጦር ትምህርት ቤት በሌላ መጠሪያም የሚታወቅ ቢሆንም ዛሬ ግን የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሚል ተሰይሟል። የዚህ ፅሁፍ የቆይታችን ማስታወሻ "የጥቁር አንበሳ አንባ" የሆነው የቀድሞው ገነት ጦር ትምህርት ቤት የዛሬው የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ነው።

የዛን ወቅት የፀረ-ፋሽስት ወረራ ተጋድሎ ጀግና መኮንኖች መፍለቂያ ግቢ የተገኘሁት ለስልጠና ነው። እኔና ከመላው የሠራዊታችን ክፍሎች የተውጣጡ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ አመራር እና የሚዲያ ሙያተኞች ነን። ስልጠናችን በዚህ የጀግኖች መፍለቂያ መሆኑ ለግባችን ስኬት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል። በጥቁር አንበሳ ጀግኖች ስነ-ልቦናችን እየተገነባ፣ በደማቅ ገድላቸው ትውስታ መንፈሳችን እየረካ ፣ እንደ እነርሱ በፈተና ፀንተን የሀገር ኩራት ተተኪዎችን በአምሳላችን የምንቀርፅበትን እድል  እንደሚኖረን አልተጠራጠርንም።

ዛሬ የጥቁር አንበሳ ጀግኖቹ በዚህ ግቢ አይኑሩ እንጂ መንፈሳቸው አልጠፋም። ታሪክና ገድላቸው በግቢው አየርና በሰው ላይ ሰፍሮ ጀግንነትን ያወርሳል። አንድነትን ፈጥሮ ውስጥን በሀገር ፍቅር ይሞላል። በእርግጥም የጀግንነታቸው ምንጩ ፣ የድላቸው ምክንያቱ ቢዳሰስ አንድነትና የሀገር ፍቅራቸው መሆኑ ጥርጥር የለውም። እኛም እዚህ የተገኘነው በአንድነት ነበር። ለአንድ አላማ ስኬትና ግብ። እናም እኔ እያልኩ ሳወጋ የስልጠናው ተካፋዮችንም ጭምር እያልኩ መሆኑ ይያዝልኝ ። ሠራዊታችንም እንዲሁ ተልዕኮና ህይወቱ የጋራ ነው፣ የግልና የተናጠል ግዳጅና ግብ አይኖረውም። ግዳጁ አንድ ፣ ግቡም የጋራ ነው። እኔም የጥቁር አንበሳ መፍለቂያ ካምፕ ቆይታዬን ሳካፍል ብዙውን እንደ አንድ በመቁጠር ነው።

የምስረታ ስሙ ገነት ጦር ትምህርት ቤት ሲሆን ዛሬ ላይ በአካዳሚነት አድጎ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የሚል ስያሜን አግኝቷል። የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ መገኛ ሆለታ ገነት ነው። ከመዲናችን አዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር አካባቢ ይሆናል። ወደ ሆለታ ገነት በምዕራብ አቅጣጫ በሁለት በኩል ከአዲስ አበባ መውጣት ይቻላል።

በቀድሞው ርቀቷ 44 ኪሎ ሜትር ተጉዘህ ወደ ግራ ስትታጣፍ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ "እንኳን ደህና መጡ" ብሎ ይቀበልሃል። እኔ ግን አዲስ አበባ የደረስኩት ከ500 በላይ ኪሎ ሜትሮችን አቆራርጭ ነው።  መነሻዬ ለህዝብና ለሀገር ሰላም መከበር ቀን ከሌት ከፅንፈኞች ጋር ከሚፋለሙ ጀግኖች ስፍራ ነው።
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የመግቢያውን በር ስዘልቅ ረዥም ሀውልት ተመለከትኩ። የሀውልቱ አናት ላይ በሰማይ እንደሚበር እርግብ የወታደር ምስል አለው። ከዚህ ቀደም ይህንኑ ሀውልት በአካልም በፎቶም አውቀው ነበር። ስለ ሀውልቱ ቅድመ-ታሪክ የሚያስረዳኝ ባልማግኘቴ ዛሬም ድረስ ጥያቄው ውስጤ አለ። 
  ከዚያስ ይቀጥላል......

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
04/22/2025, 10:48
t.me/fdredefenseforc/38875
በሠራዊታችን አኩሪ ተጋድሎ የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጂት መሥራት ያሥፈልጋል፡፡
  ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን
         
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ማያዚያ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት እናረጋግጥ በሚል ምክረ ሀሰብ ከሀገር ሽማግሌዎች፤ከሀይማኖት አባቶች እና ከአካባቢው መህበረሰብ ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡
         
ውይይቱን የመሩት የ6ኛ ዕዘ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል በርሃኑ ጥላሁን ሠራዊታችን ሌት ተቀን እረፍት የለሽ ግዳጅ እየተዋጣ እና የህይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የሚገኘዉ ሀገራዊ ሰላምን ለማረጋገጥ እና ህዝብም የተሟላ ሰላም አግኝቶ ፊቱን ወደ ልማት እንዲያዞር ለማስቻል ነው ሲሉ ገልፀዋል ፡፡

በወረዳው የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ሀይሎች በሰራዊታችን እና በህብረተሰቡ ብርቱ ክንድ ተመትተው ሰጋት ወደማይሆኑበት ደረጃ መድረሳቸውን ሜጀር ጀነራል በርሃኑ ጥላሁን ተናግረዋል፡፡
        
የደራ ህዝብ የመቻቻል እና የመከባበር እሴቱን አዳብሮ በአብሮነት እና በፍቅር የኖረ መልካም ህዝብ ነው ያሉት ሜጀር ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ይህንኑ ለዘመናት የዘለቀውን መልካም እሴት እና አብሮነት ለማፍረስ የሚጥሩ የጥፋት ሀይሎችን ከሰራዊታችን ጋር በመሆን መታገል ህዝቡ እንደሚጠበቅበት አሥረድተዋል፡፡
         
የደራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ታዬ በበኩላቸው በወረዳው አሁን የተገኘው አንፃራዊ ሰላም በሰራዊታችን የተከፈለ መስዋዕትነት በመሆኑ ለዚህ ከምንም በላይ ትልቅ ምስጋና አለን፤ የተጀመሩ የመሰረተ ልማት እና የመልካም አሳተዳደር ስራዎችን ማስቀጠል ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይጠበቃል ሲሉ አመላክተዋል።
         
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩልቸው አሁን ባገኘነው ሰላም ያተረፍነው ቡዙ ነገር ነውና በጫካ ያሉ ሀይሎችም ወደ ሰላም እና ውይይት በመምጣት የሀሳብ ታጋይ መሆን እንዳለባቸው ገልፀው እነሱም እንደ ማህበረሰብ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
    
ዘጋቢ ደባልቅ አቤ
ፎቶ ግራፍ ሰው መሆን ሀብቱ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/21/2025, 15:15
t.me/fdredefenseforc/38873
መቻል እግር ኳስ ቡድን አዳማ ከተማን በማሸነፍ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን አሳክቷል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

በሀያ ስድስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪምየር ሊግ መቻል አዳማ ከተማን 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን አስመዝግቧል።

ለመቻል የመሸነፊያ ሁለቱንም ጎሎቹን ሽመልስ በቀለ  ከመረብ አሳርፏል።

የመቻል 18 ቁጥር ለባሹ ሽመልስ በቀለ መቻል ተከታታይ ሶስት ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ አራት ወሳኝ  ጎሎችን በማስቆጠር ቡድኑን ወደ ድል እንዲመለስ አድርጎታል።

ድሉን ተከትሎ መቻል እግር ኳስ ቡድን ነጥቡን 38 በማድረስ 3ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል። ፕሪምየር ሊጉን ኢትዮጵያ መድህን ሲመራ ፣ ኢትዮጵያ ቡና ሁለተኛ መቻል ሶስተኛ ፣ ባህርዳር ከተማ አራተኛ ደረጃ በመያዝ እየተፎካከሩ ይገኛሉ።

ውድድሩ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታድየም የሚቀጥል ይሆናል።

ዘጋቢ ገረመው ጨሬ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/21/2025, 11:43
t.me/fdredefenseforc/38869
በፅንፈኛው እና በሽብር ቡድኖች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጥሏል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

በሰሜን ሸዋ ባሶና ወረዳ የሚንቀሳቀሰው ፅንፈኛ ታጣቂ ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተመትቷል።

ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ፅንፈኛውን ፋኖ ከገባበት ገብቶ አየገረፈው ነው። በዚህም ሠራዊቱ በአንድ ቀን በጎጃም ብቻ ባደረገው ኦፕሬሽን መንበሩን ጨምሮ ከ300 በላይ ታጣቂዎችን እስከወዲያኛው ሸኝቷል።

ትላንት ወደአመሻሽ ደግሞ በሰሜን ሽዋ ዞን ባሶና ወረዳ ካሲማ በተባለ ቦታ ሠራዊቱ ባደረገው ኦኘሬሽን 4 የቡድኑን መሪዎች 50 ከሚሆኑት ታጣቂዎቻቸው ጋር ሸኝቷቸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ 30 የሚሆኑት ጉዳት አስተናግደው ተማርከዋል። ከኦፕሬሽኑ 3 ብሬን፣ 5 ስናይፐር እና በርካታ ቡድኑ ታጥቋቸው የነበሩ መሳሪያዎች ገቢ ሆነዋል። ሰራዊቱ አሁንም ከምቱ ተርፎ የፈረጠጠውን ፅንፈኛ መልቀሙን ቀጥሏል።

በተመሳሳይ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በቱቲ ቀበሌ ሆሞ ቦነያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሠራዊቱ ባደረገው የተቀናጀ ስምሪት የፅንፈኛውን ቡድኑን ማሰልጠኛ በመቆጣጠር ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ መቻሉን የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮ አስታውቀዋል።

በሌላ ዜና የምዕራብ ዕዝ ክፍለጦር  በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ ቆናጮና ባቅላ ቀበሌ ባደረገው የተጠናከረ ዘመቻ የሸኔ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል። በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳዎች ላይ በሚገኙ ቀበሌዎች  የሽብር ቡድኑ የአካባቢውን ሰላም ለማደፍረስ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን መከላከያ በወሠደው እርምጃ ምርኮኞ ሙትና ቁስለኛ ለመሆን ተገዷል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 20:50
t.me/fdredefenseforc/38865
https://youtu.be/2Yz9GLUi8rw?si=22ZNClef0xbYY_0D
04/20/2025, 18:11
t.me/fdredefenseforc/38859
የደቡብ ጎንደር እና ጎጃም ለሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት 111 በሬዎችን ድጋፍ ተደርጓል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

በአማራ ክልል ጎጃምና ደቡብ ጎንደር ዞን ለተሰማሩት ኮሮች  111 የእርድ በሬዎችን፣ በርካታ በጎችና ፍየሎች ድጋፍ ተደርገዋል።

በአማራ ክልል ሙሉ ጎጃምና ደቡብ ጎንደር ተሰማርቶ ግዳጁን በአስተማማኝ እየተወጡ ለሚገኙት የሠራዊታችን ክፍሎች የተደረገላቸው ድጋፍ ህብረተሰቡ ከሰራዊቱ ጎን እንደሆነና አለኝታነቱን በተግባር ያስመሰከረ ድርጊት መሆኑ ተመልክቷል።

ለሠራዊቱ ድጋፍ መደረጉን ያመስገኑት በየቀጣናው ድጋፉን የተቀበሉት አመራሮች ፣ ሰራዊቱ አንድ ህይወቱን ሳይሰስት መስዋዕትነት በመክፈል የክልሉን ሰላም ወደ ነበረበት እንዲመለስ ግዳጁን በተገቢው መንገድ እየተወጣ እንደሚገኝ አውስተው ለተደረገው ድጋፍ ለህዝቡ ምስጋና አቅርበዋል።

ህዝቡ የሰጠው ድጋፍ ፣ ሠራዊቱ አየከፈለ ላለው መስዋዕትነት እና ለተገኘው ሠላም እውቅና የሰጠበት ነው ያሉት አመራሮቹ ፣ ህዝቡ ፅንፈኛው በማጥፋት ከሰራዊቱ ጎን መሆናቸዉን ያረጋገጠበት መሆኑን አመልክተዋል።

ሰራዊቱ በየጊዜው የሚፈፅማቸውን ገድሎች በማጠናከር ቀጣይም አኩሪ ግዳጆችን እንድንወጣ ህዝባችን እንደወትሮው ሁሉ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ለቀጠናው ሰላም በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

ዘጋቢ አወል መሃመድ
ፎቶግራፍ ኮሮች

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 14:31
t.me/fdredefenseforc/38858
የተንሳኤን በዓል አሥመልክቶ ለመከላከያ ሠራዊት የእርድ እንሰሳት ድጋፍ ተደርጓል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የደቡብ ወሎ ዞን ሕዝብ ለትንሳኤ በዓል መዋያ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸውን የእርድ እንስሳት ለመከላከያ ሠራዊትና ለአካባቢ ፀጥታ ኃይል አበርክቷል፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን የደቡብ ወሎ ዞን ሕዝብ ለእኛ ሰላም ብለው ዋጋ እየከፈሉ ያሉት የመከላከያ ሠራዊቱና ሌሎች የአካባቢ የፀጥታ ኃይሎች የትንሳኤ በዓልን በሰላምና በደስታ እንዲያሳልፉ በሚል ግምታቸው ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆኑ 43 በሬ፣186 የበግና የፍየል ሙክቶችን አበርክተዋል ብለዋል።

የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ኮር ዘመቻ ሀላፊ ሻለቃ መላኩ ቶላ የተደረገው የእርድ እንስሳት ድጋፍ ሰራዊታችን እና ሕዝቡ ያለውን ትስስርና አንድነት የበለጠ ከማጠናከሩም በላይ ለቀጣይ ተልዕኮ የሚያነሳሳ በመሆኑ በተደረገውም ድጋፍ ሰራዊታችን በእጅጉ ደስተኛ ነው ሲሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ዘጋቢ ካሳሁን ስመኘው ነው

በተመሳሳይ የምዕራብ ሸዋ ዞን ጅባት ወረዳ በግዳጅ ላይ ለሚገኙ የሠራዊቱ አባላት የእርድ ሰንጋዎችን አበርክቷል። ድጋፉን የተረከቡት የፅናት ክፍለጦር አዛዥ ፅህፈት ቤት ሃላፍ ሌተናል ኮሎኔል ወንደሰን ባዩ ሠራዊቱ የህዝብን ሠላም የሚነሱ አካላትን ከወረዳው በማፅዳት ህብረተሰቡ የሠላም አየር እንዲተነፍስ ቀን ከሌሊት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሰርበሳ ታፈሰ ሠራዊቱ በዱር በገደሉ የሽብር ቡድኑን እረፍት በመንሳት ወረዳውን ወደ ተረጋጋ ሠላም በመመለስ ህዝቡ ያለምንም ስጋት በአሉን እንዲያሳልፍ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ዘገባው የፍቃዱ አበራ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 14:19
t.me/fdredefenseforc/38852
የስፖርት ፌስቲቫሉ የምስረታ በዓላችንን ጅማሮ ያበሰረና የሠራዊታችንን አቅም ያሳዬ ነው።
     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

ምዕራብ ዕዝ 47ኛ አመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግና የዕዙን ምርጥ ስፖርተኞች ለመለየት በነቀምት ከተማ ያካሄደው ስፖርታዊ ፌስቲቫል በደማቅ ስነ-ስርዓት ተጠናቋል።

በመዝጊያ ስነ- ስርዓቱ ላይ የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት፣ የምስራቅ ወለጋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስፋው ሚዴቅሳ እንዲሁም የኮር አመራሮችና መምሪያ ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ለአንድ ሳምንት በቆየው ስፖርታዊ ውድድር የሰራዊታችን የእችላለሁ መንፈስ ጎልቶ የታየበትና ፈተናን በፅናት መወጣት እንደሚቻል ያሳዩበት እንደሆነም ተገልጿል።

ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት ያካሄድነው የስፖርት ፌስቲቫል የዕዛችንን የምስረታ በዓል ጅማሮ ከማብሰሩም ባለፈ ተቋማችን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች መገኛ  የእምቅ አቅሞች መፍለቂያ መሆኑንም አሳይቷል ብለዋል።

ህዝባዊና ህገ-መንግስታዊ ተልዕኳችሁን ሳትዘነጉ ከመደበኛ ግዳጃችሁ ጎን ለጎን ራሳችሁን በስፖርት ተወዳዳሪና ብቁ ማድረጋችሁ እጅግ የሚመሰገን ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት በቀጣይም ተቋሙ ለሚያዘጋጀው ውድድር ከወዲሁ ራሳችሁን እያበቃችሁ መጠበቅ ይኖርባችኋል ብለዋል።

አሸናፊ ለሆኑ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት ያበረከቱት ጄኔራል መኮንኑ ሰራዊት ምንጊዜም ማሸነፍን ግብ አድርጎ መንቀሳቀስ እንዳለበት ሁሉ ስፖርትም ማሸነፍን ብቻ ግብ ካላደረጉ ዋንጫ የማንሳት እድልን እንደማይሰጥ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ለፌስቲቫሉ መሳካት ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች ምስጋና አቅርበዋል።

ከተወዳዳሪዎች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት ስፖርታዊ ውድድሮች ለእርስ በእርስ ትውውቅና ጓዳዊ ዝምድና የሚኖረው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ጠቁመዋል።

ዘጋቢ ሰማሀኝ ጥላሁን
ፎቶግራፍ አከለ አባተ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 13:47
t.me/fdredefenseforc/38848
የ19 ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ አዛዡ ጁባ የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ሻምበል ጎብኝተዋል። 

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 3017 ዓ.ም

በደቡብ ሱዳን ጁባ የ19ኛ ሠላም አሥከባሪ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል አለሙ ኪንኪና ሻለቃው ከዌስተርን ኢኳተሪያ በተጨማሪ በቅርቡ ጁባ አካባቢ የሚስተዋለውን ስጋት ለመቅረፍ በዮናሚስ ግዳጅ የተረጣቸው ሲሆን የሰላም አስከባሪ ሻምበሉ  ወቅታዊ የግዳጅ አፈፃፀምና ወታደራዊ ዝግጁነት የሚገኝበት ደረጃ አመርቂ መሆኑ መረዳታቸውን ተናግረዋል።

ኮሎኔል አለሙ የሻለቃው የግዳጅ ቀጠና ከሆነው ከሴክተር ሳውዝ በተጨማሪ ሴክተር ጁባ ያቀረበውን ጥያቄ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ግዳጁ የ19ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ብቸኛው በዮናሚስ በሁለት ሴክተሮች የሚመራ ይህም የግዳጅ አፈፃፀሙ  የላቀ መሆኑንና ተመራጭንቱን የሚያመላክት እንደሆነ ተናግረዋል::

የሻለቃዋ ተልዕኮ ሲቪሎችን ከማንኛውም ጥቃት መከላከል መሆኑን የጠቆመት ኮሎኔል አለሙ  ሰላም አስከባሪ ሻምበሉ ሊከሰቱ የሚችሉ ክስተቶችን በንቃት የመከታተል ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባውም አስገንዝበዋል።

ሻለቃዋ በቆይታዋ ላስመዘገበችው የላቀ ግዳጅ አፈፃፀምና በሲሚክ ሥራዎች ላበረከተቻቸው የላቀ አስተዋፅዖ በዩናሚስ እውቅና መስጠቱን የገለጹት ኮሎኔል አለሙ ኪንኪና ሃገርንና ተቋምን የሚያኮራ ለገፅታ ግንባታውም ሚናው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።

የ19ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ የተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ግጭቶች የሚስተዋሉበትና ተፈጥሯዊ መስናክሎች የተበራከቱበት ቢሆንም በሁኔታ ወቅት ፈጥኖ በመድረስ በደቡብ ሱዳን ብቻ ሳይሆን አለም ላይ ከተሰማሩት ሰላም አስከባሪ ሻለቆች በቀዳሚነት ተጠቃሽ መሆን በመቻሉም የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።

የ19ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ  ዩናሚስ የሚተማመንበት ኢትዮጵያዊ የሰላም ማስከበር ሻለቃ በመሆኑም የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ለውጤቱ  መመዝገብ ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው የሻለቃው አመራርና አባላት  ምስጋና አቅርበዋል።

ዘጋቢ አምታታው ከበደ
ፎቶግራፍ ዮዲት ብዙ ወርቅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 11:55
t.me/fdredefenseforc/38842
ህዝቡ ሠንጋ በማበርከት ለሠራዊቱ ያለውን ድጋፍ አረጋግጧል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዝያ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የሰሜን ሸዋ ዞን ደራ  ወረዳ አስተዳደር የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ በቀጠናው ተልዕኮውን እየፈፀመ ለሚገኘው የ6ኛ ዕዝ መከታ ክፍለ ጦር 12 የዕርድ ሰንጋዎችን እና 01 ሙክት በስጦታ አበርክቷል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ታዬ የተደረገው ድጋፍ ሰራዊቱ በአካባቢው የነበረውን የፀጥታ ችግር በከፈለው የህይወት መስዋዕትነት እና ጀግንነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በመቀልበስ ላረጋገጠው ሰላም ያለንን አጋርነት እና ምስጋና ለመግለፅ እና ከሰራዊቱ ጎን መሆናችንን ለማሳየት እንጅ ከተልዕኮው አንፃር በቂ ሁኖ አይደለም ብለዋል።

ድጋፉን  የተረከቡት የክፍለ ጦሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ድልነካ ከድር ሰራዋቱ በቀጠናው ላይ የህዝብን ሰላም እና ደህንነት በማረጋገጥ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት እየፈፀመ እንደሚገኝ ገልፀው፤በቀጣይም ዘላቂ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት እና ከህዝብ ጋር በመሆን ተልዕኳችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ነው ያሉት። ለተደረገው ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዘጋቢው ደባልቅ አቤ ነው
     
በተመሳሳይ በምዕራብ ሽዋ ዞን የሜታ ውልቂጤ ወረዳ  በቀጠናው ተሰማርቶ ግዳጁን እየተዋጣ ለሚገኘው  ለ6ኛ ዕዝ መብረቅ ክፍለጦር የእርድ ሰንጋዎችንና  ፍየሎችን ድጋፍ አድርጓል ።

‎ ድጋፉን የተረከቡት የክፍለ ጦሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት  ኮሎኔል ደረጄ ሶሪ የከተማ አስተዳደሩ በተለያየ ጊዜ ለሠራዊቱ እያደረገ ያለውን ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን በማውሳት አሁንም የፋሲካ በዓልን አስመልክቶ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

‎ድጋፍ ያበረከቱት የሜታ ውልቂጤ ወረዳ አስተዳደር አቶ ብርሀኑ ሀንጅማ መከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም እና ፀጥታ በማስከበር ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ህዝባችን በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ እያደረገ ያለው መስዋዕትነት በምንም መልኩ መተኪያ ባይገኝለትም በዓሉን እንዲያከብር ይህን የእርድ ሰንጋዎችን ድጋፍ አበርክተናል ብለዋል። ዘጋቢው ሰይድ አደም ነው
‎ 
‎የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/20/2025, 08:01
t.me/fdredefenseforc/38839
ለመከላከያ ሠራዊቱ የሚደረገው የበዓል ስጦታ እንደቀጠለ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

በሰሜን ወሎ ዞን ተሰማርቶ ግዳጁን እየተወጣ ለሚገኘው የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መተማ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት የዋድላ ወረዳ ከተማ አስተዳደር እና የሙጃ ከተማ ህብረተሰብ በአሉን አስመልክቶ የእርድ በሬዎችንና በጎችን በስጦታ አበርክቷል።

ስጦታውን የተረከቡት የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ደመወዝ መንግስቴ ህዝባችን ሁልጊዜም ቢሆን ከጎናችን በመሠለፍ ለሚያደርግልን ድጋፍ ሁሉ በሰራዊቱ ስም የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ሲሉ ተናግረዋል። ዘገባው የፈንታሁን ንጉስ ነው

በተመሳሳይ የምዕራብ ወለጋ ዞን የጊንቢ ከተማ መስተዳድር የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ለዕርድ የሚሆኑ ሰንጋ በሬዎችን ለሰራዊቱ በስጦታ መልክ አበርክተዋል።

በድጋፉ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ የተገኙት የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ ለሰራዊታችን የምናደርገው ማንኛውም ድጋፍ አገራዊ ግዴታችን በመሆኑ አጠናክረን እንቀጥልበታለን በማለት ተናግረዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የግቤ ኮር ምክትል አዛዥ ለውግያ ድጋፍ አገልግሎት ተወካይ ሌተናል ኮሎኔል ጋረደው ጋልዳ የዞኑ ማህበረሰብ እና መስተዳድር ለሰራዊታችን በየጊዜው እያደረጉት ያሉት ድጋፍና ትብብር የሚደነቅ  እና የሚመሰገን ተግባር ነው ብለዋል።
 
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 20:47
t.me/fdredefenseforc/38835
የተቋሙ መለያ የሆነው መቻል ስፖርት ክለብ  የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማደረግ ድጋፍ አደረገ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

መቻል ስፖርት ክለብ የፋሲካ በአልን ምክንያት በማድረግ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ለሚኖሩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።

በፕሮግራም ላይ በመገኘት ደጋፉን የሠጡት የመቻል ስፖርት ክለብ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ፌበን አበራ በጋራ በመሆን ነው።

ስፖርት ክለቡ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ ሁሌም ከህዝቡ ጎን ነው ያሉት የመቻል ስፖርት ክለብ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን አባላቱ  ህዝባዊነታቸውን ለማሳየት ከኪሳቸው በማዋጣት የዛሬውን ማዕድ ማጋራታቸውን ገልፀዋል።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ፌበን አበራ ሠራዊታችን ለሀገር እና ለህዝባችን ህይወቱን ከመስጠቱ ባለፈ ካለው ላይ በመቀነስ ድጋፍ
በማድረጉ ትልቅ ክብር አለን ብለዋል።

ዘጋቢ ገረመው ጨሬ
ፎቶግራፍ እስክንድር ሰለሞን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 18:06
t.me/fdredefenseforc/38832
ተልዕኮውን እየፈፀመ ለሚገኘው ሠራዊት ለትንሳኤ በዓል የበሬ እና የበግ ድጋፍ ተደርጓል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መርሐቤቴ ወረዳ ህብረተሰቡ ለሠራዊቱ 350 ሺህ ብር የሚገመት 05 ሰንጋዎች እና ለአስቤዛ የሚውል 75 ሺህ ብር መለገሳቸውን የአየር ወለድ ክፍለ ጦር የጥገና ቡድን ሃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ግዛቸው አቦዬ ተናግረዋል።

በመርሐቤቴ ወረዳ የዓለም ከተማ አስተዳዳሪ አቶ ያቤፅ ንጉሴ በበኩላቸው ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ለህዝብ እና ለሀገር ሠላም ውድ ህይወቱን አሳልፎ በመስጠት ላይ ለሚገኘው ሠራዊት አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርገለን ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል። ዘገባው የአየር ወለድ ክፍለጦር የሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ነው።

በተመሳሳይ በሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር ፋይናንሰ ሃላፊ ሻምበል ሙዘሚል ጠሃ የደባርቅ ህዝብና መስተዳድር ለሠራዊቱ ያለውን ክብርና ፍቅር ለመግለፅ ለትንሳኤ በዓል ያበረከተውን የበግና የሠንጋ ድጋፍ ተረክበዋል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ ከንቲባ አቶ ልዑል መስፍን እና የደባርቅ ከተማ ፀጥታ ሃላፊ አቶ ዘመን እዱኛ የመከላከያ ሠራዊት የሀገር መከታ የሆነ ሀገር ክበርና ዝናዋን ጠብቃ እንድትቀጥል ለህዝባችን ህይወቱን እየሰጠ የመጣ ሠራዊት በመሆኑ ዛሬ ለትንሳኤ በዓል የበሬ ሰንጋ እና የበግ ድጋፍ ለሠራዊታችን ካልን አካፍለን ስንሰጠ ታላቅ ደሰታ ይሰማናል ሲሉ ተናግረዋል። ዘጋቢ ያውነው አየለ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 17:06
t.me/fdredefenseforc/38829
የተንሳኤን በዓል አሥመልክቶ ለሠራዊቱ የእርድ ሠንጋ እየተበረከተ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

የሰሜን ሽዋ ዞን የሂደቡ አቦቴ ወረዳ አስተዳደር ለሠራዊቱ ለተንሳኤ ባዕል ምክንያት በማድረግ የእርድ ስንጋ ድጋፍ ማድረጉን የ6ኛ ዕዝ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ሞገስ አሰልፍ ተናገሩ።

ሰራዊቱ የተሰጠውን ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በላቀ ቁርጠኝነት እየፈፀመና የአካባቢውን ሰላም ወደ ነበረበት የመመለስ ተልዕኮውን በሚገባ እየተወጣና በመወጣት ላይ እደሚገኝ የገለፁት ሃላፊው ወረዳው በአካባቢው እየተስተዋለ በመጣው ሰላም ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን 05 የእርድ ስንጋ ድጋፍ በማድረግ አረጋግጧል ብለዋል።

ሁሌም ለህዝብና ለሃገሩ ሰላም ሲል በዱር በገደሉ እየወጣና እየወረደ በቁርጠኝነት ሰላም ለሚያስከብረው ሰራዊታችን በችግር ብቻ ሳይሆን በደስታችንም ከጎኑ በመቆም የበኩላችንን አስተዋፅኦ እንወጣለን ያሉት የሰሜን ሽዋ ዞን የሂደቡ አቦቴ ወረዳ አሥተዳደር አቶ አሸብር ሂደቡ ናቸው። ዘገባው የውበቴ አማረ ነው

በተመሳሳይ በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ግዳጅ እየፈፀመ ለሚገኘው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ክፍለ ጦር የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዕርድ ሰንጋዎች  ተበርክቶለታል።

ድጋፉን የተረከቡት የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ገብረ-እግዚሄር ብርሃነ ሰራዊታችን የተሰጠውን ሀገራዊ ተልእኮ እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ድጋፍ ህብረተሰቡ ለሠራዊቱ ያለውን ህዝባዊነት ያረጋገጠበት ነው ብለዋልል። ለተደረገው ድጋፍ በክፍለ ጦሩ የሰራዊት አባላት ስም ምስጋና አቅርበዋል።
   
ድጋፉን ያስረከቡት የቋራ ወረዳ ተወካይ አስተዳደር አቶ ወርቁ አስማማው ለሠራዊታችን ታላቅ ክብር አለን ወደፊትም ድጋፋችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል። የዘገበው ብርሃኑ ነጋሳ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 15:17
t.me/fdredefenseforc/38826
ጠንካራ ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነቱን በስልጠና ያረጋገጠ ሰራዊት በሚሰጠው ተልዕኮ ሁሌም አሸናፊ ነው
  ሜጄር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በማዕከላዊ ዕዝ ተገኘተው በስልጠና ላይ ለሚገኙ አመራሮች የሥልጠና ማጠቃለያ በመሥጠት የህይወት ተሞክሯቸውን አካፍለዋል።

ጀኔራል መኮንኑ በቆይታቸው ለሳምንታት በተሰጡ ትምህርቶች ላይ ማጠቃለያ በመስጠት በተለይም በሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ ዙሪያ ሰፊ ትምህርትና ማብራሪያ በማድረግ ለተተኪ አመራሩ አስፈላጊ ቁምነገሮችን አስጨብጠዋል።

የሰራዊት ግንባታ የሁሉንም ሃላፊነት የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን በትምህርታቸው ያነሱት ሜጄር ጀኔራል እንዳልካቸው አመራሩ የሚመራቸውን አባላቶች በየዘርፉ በመገንባትና በማብቃት ተቋሙን የሚወድና ህዝብን በቅንነት የሚያገለግል ተልዕኮውን የተረዳና ግዳጁን በዕውቀት ላይ ተመስርቶ የሚፈፅም ጠንካራ ስነ ልቦና ያለው ወታደር የመገንባት ሃላፊነት አለበት ሲሉ አስረድተዋል።

የሰራዊቱን ስም በማጠልሸት ጀግንነቱን በማጣጣልና ለሃገር የሚከፍለውን ክቡር መስዋዕትነት በማንኳሰስ እኩይ ተልዕኳቸውን ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ ሃሰተኛ ሚዲያዎችን ለይቶ በማወቅ ከጠላት የሃሰት ፕሮፖጋንዳ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ያስገነዘቡት ጀኔራል መኮንኑ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ እውነት ግሃድ በማውጣት የሰራዊቱን ዘመን አይሽሬ ገድል መልሶ ለግንባታ ስራ መጠቀም በቀጣይ ከአመራሩ የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል።

ማዕከላዊ ዕዝ በየደረጃዉ የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ዘመኑን የዋጀ አስተማማኝ የሃገር ዘብ ለመፍጠር የሚያደርገውን ያላሰለሰ ጥረት ያደነቁት ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ስልጠናውን በየደረጃው መደገፍና ተፈላጊው ግብ ላይ ማድረስ ሁሉንም የሚመለከት ተቋማዊ ሃላፊነት ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ስልጠናው አሁን ላይ ከጓድ እስከ ሬጅመንት አመራር ድረስ በዕዝ ደረጃ እየተሰጠ ሲሆን በሁሉም ኮሮችና ክፍለ ጦሮች በየስራ ዘርፉና በየመሳሪያ ምድቡ የሚሰጡ ተመሳሳይ ስልጠናዎች ከግዳጅ ጎን ለጎን ተጠናክረው ቀጥለዋል።

ዘጋቢ ኤፍሬም አድማሱ
ፎቶግራፍ ከማሰልጠኛ ማዕከሉ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 14:52
t.me/fdredefenseforc/38821
ለክፍለ ጦሩ የትሳኤን ባዕል ምክንያት በማድረግ ለሠራዊቱ የእርድ ስንጋ ድጋፍ ተደረገ።

የኢፊዲሪ መከላከያ ሰራዊት ሚዚያ 11ቀን 2017ዓ/ም

የ6ኛ ዕዝ ጋሻ ክፍለ ጦር በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጠና የሰሜን ሽዋ ዞን የሂደቡ አቦቴ ወረዳ አስተዳደር ለሠራዊቱ ለተንሳኤ ባዕል ምክንያት በማድረግ የእርድ ስንጋ ድጋፍ ማድረጉን የክፍለጦሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ሞገስ አሰልፍ ተናገሩ።

ሰራዊቱ የተሰጠውን ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በላቀ ቁርጠኝነት  እየፈፀመና ያካባቢውን ሰላም ወደ ነበረበት የማስመለስ ተልዕኮውን በሚገባ እየተወጣና በመወጣት ላይ እደሚገኝ የገለፁት ሃላፊው ወረዳው በአካባቢው እየተስተዋለ በመጣው ሰላም ከሰራዊቱ ጓን በመሰለፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እደሚገኝ ገልፀዋል።

ከፍተኛ መኮነን አክለውም የወረዳው መስተዳድር ሰራዊቱ የተንሳኤን ባዕል ባለበት በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና በሚገባ ማክበር አለበት በማለት 05የእርድ ስንጋ ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ሁሌም ለህዝብና ለሃገሩ ሰላም ሲል በዱር በገደሉ እየወጣና እየወረደ በቁርጠኝነት  ሰላም ለሚያስከብረው ሰራዊታችን በችግር ብቻ ሳይሆን በደስታችንም ከጎኑ በመቆም የበኩላችንን አስተዋፅኦ እንወጣለን ያሉት የሰሜን ሽዋ ዞን የሂደቡ አቦቴ ወረዳ መስተዳደር አቶ አሸብር ሂደቡ ናቸው።

በመጨረሻም የወረዳው መስተዳደር ከሰራዊቱ ጓን በመሰለፍ በአካባቢው ለመጣው ሰላም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ  እያበረከተ እደሚገኝና አአሁንም ለማንኛውም ግዳጅ ከሰራዊቱ ጓን በመሰለፍ እንዋጣለን ሲሉ የወረዳው መስተዳደር ተናግረዋል።
  

ዘጋቢ ውበቴ አማረ
ፎቶ ግራፈር ከክፍሎች
04/19/2025, 14:52
t.me/fdredefenseforc/38820
የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለሠራዊቱ አባላት የሚደረገው ድጋፍ ቀጥሏል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

የላይኛው አዋሽ አግሮ ኢንዱስትሪ ፋብሪካ ሀገራዊ ግዳጃቸውን በመወጣት ላይ ላሉ የመከላከያ ሰራዊትና ለፌዴራል ፖሊስ የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ግምታቸው 270 ሺህ ብር የሚሆኑ ሰንጋዎችን ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን ያስረከቡት የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ከፊያለው ቱሉ ሰራዊታችንና የጸጥታ አካላቱ በጥምረት ለሚያደርገው ሀገራዊ ግዳጅ በተለያዩ የአመታዊ በዓሎችና ሌሎች ተመሳሳይ ፕሮግራሞች ላይ  ከጎኑ በመሆን እየፈጸሙት ላለው ተልእኮ እኛም በምንችለው መንገድ ለማገዝ ስንል የፋሲካ በዓልን በማስመልከት የሰንጋ ከብቶችን ድጋፍ አድርገናል ተብለዋል።

የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አባዲ ልዑል ሰራዊታችንና የፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ከሌሎች የጸጥታ አካላት የሲቭል ማህበረሰብ ጋር በመጣመር የተሰጠውን ሀገራዊ ተልእኮ እየተወጣ ነውና ድርጅቱ ላደረገልን ድጋፍ በመላው የክፍለ ጦሩ የሰራዊት አባላት ስም ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው ብለዋል ዘገባው የብርሃኑ ሁነኝ ነው

በተመሳሳይ በምስራቅ ሽዋ ዞን አቃቂ ወረዳ ለአንድ ክፍለ ጦር ለበዓል መዋያ  ከ150 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸውን ሰንጋዎች ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፋን የተረከቡት የክፍለጦሩ ዘመቻ ኃላፊ ሻለቃ አንዋር መሃመድ ክፍሉ ቀጠናውን ከመረከቡ በፊት አሸባሪው ሸኔ ትምህርት ቤቶችን መኖሪያ ካምፕ ክኒሊኮችን ለራሱ የግል አላማው ማስፈፀሚያ አድርጎ ለበርካታ ጊዚያት ግለሰቦችን እያፈነ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየተቀበለ ህብረተሰቡን ሲያሰቃይበት እንደነበር ገልፀው ሰራዊቱ በቦታው ከተሠማራ በኋላ ሁሉም የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ወደ ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ብለዋል። ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።

ድጋፍን ያስረከቡት የምስራቅ ሸዋ ዞን የአቃቂ ወረዳ አስተዳድር አቶ ቤካም ቱራ  ሰራዊቱ ከህዝብ የወጣ ለህዝብ የሚተጋ በመሆኑ ሰላም ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን በልማቱም የሚሳተፍ መሆኑን ገልጸው ይህ ድጋፍ ከሰራዊቱ ጎን መሆናችን እና እንደማበረታቻ እንዲሆን በማሰብ ለበዓሉ  ከማህበረሰቡ የተወጣጣ ድጋፍ እንደሆነ ገልፀዋል። ዘገባው የአብራራው ፈንቴ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/19/2025, 12:01
t.me/fdredefenseforc/38809
የሠራዊታችን ክፍሎች የተንሳኤን በዓል አሥመልክተው ድጋፍ እያደረጉ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ በሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ አስተባባሪነት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ማዕድ አጋርቷል።

በማዕድ ማጋራቱ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ በጀትና ፕሮግራም ኃላፊ ኮሎኔል ምህረት ሽፈራው ህብረተሰቡን ማገዝ፣መደገፍና መርዳት የሠራዊታችን መለያ ባህሪ የሆነው ዕሴት መገለጫ ነው የዛሬውም ማዕድ የማጋራት ፕሮግራም የህዝባዊ ወገንተኝነታችን ማሳያም ነው ብለዋል።

በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ  መሠረታዊ የፍጆታ
ሸቀጦች ዘይት፣ ስኳር፣የዕርድ ሰንጋ እንዲሁም ለ22 እማወራዎች ለእያንዳንዳቸው የ10ሺህ ብር ጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ በጀትና ፕሮግራም ኃላፊ ኮሎኔል ምህረት ሸፈራው ወደፊትም አቅም በፈቀደ መጠን ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ዘገባው የአለምፀሃይ ተሾመ ነው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ማህበራዊ ጥናቶች ኮሌጅ በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሞጆ ከተማ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ  ለአቅመ ደካማ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አድርጓል።

በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ የኮሌጁ የምርምርና ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ዲን ኘሮፌሰር  ተጫነ ተፈራ ኮሌጁ ሰራዊቱን ከማዘመን እንዲሁም በክህሎትና በዕውቀት ብቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢው ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የመደገፍና በጋራ የመስራት አላማ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የሞጆ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ምንዳኤ ሚደቅሳ ሰራዊቱ ለህዝብ እና ለሃገሩ ህይወት ከመስጠት ባለፍ እያደረገ ያለው ተግባር ከህዝባዊ ፍቅር እና ከሀገር ወዳድነቱ የሚነሳ በመሆኑ ኮሌጁም ይህን በተግባር አረጋግጧል ብለዋል ዘገባው የኮሌጁ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ቡድን ነው ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 16:09
t.me/fdredefenseforc/38806
ሠራዊቱ በዓልን አሥመልክቶ ድጋፍ ለሚገባቸው ወገኖች ድጋፍ እያደረገ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢፌዴሪ አየር ኃይል የሰራዊት ስነ ልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ኮሎኔል ተሾመ በዳዳ በድጋፍ መርሀ ግብሩ ላይ ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ ከመወጣት ባሻገር በየክብረ በዓላቱ እገዛ ለሚያሻቸው ወገኖች ድጋፍ ሲያደርግ እንደመጣና በሰብአዊነት ተግባራት ላይም በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልፀው ከሰራዊታችን መልካም እሴቶች መሀል አንዱ የሆነውን ይህን የበጎ ተግባር አርዓያነት ያለው ስራ ለወደፊቱም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የአየር ኃይል ወታደራዊ መደብሮች እና መዝናኛ ክበባት ኃላፊ ኮሎነል ንጉሴ ለማ ከዛሬው ልዩ የበዓል ስጦታ በተጨማሪ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ የእርድ ከብቶችን  ዶሮና እንቁላል ጤፍ የፉርኖ ዱቄት አትክልት እና ፍራፍሬን ጨምሮ ሌሎችንም አስፈላጊ የበዓል ምርቶችን እስከ 30 ፐርሰንት ቅናሽ ለተቋሙ አባላት ያቀረበ መሆኑንም ገልፀዋል። ዘገባው የፍቅሬ በቀለ ነው

በተመሳሳይ የኮማንዶ ሬጅመንት የሠራዊት አባላት ለአንድ የአረጋዊያን መርጃ ማዕከል ከኪሳቸው በማዋጣት ሃያ ሺህ ብር በጥሬ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

ሠራዊቱን በመወከል ድጋፉን ያበረከቱት የሬጅመንቱ አዛዥ ሻለቃ ታሪኩ ሻሜቦ ሠራዊቱ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ ሁሌም ከህዝቡ ጋር በመሆኑ ከህዝባዊነት ባህሪው በመነጨ አስተሳሰብ ካለችዉ ትንሽ ገቢ ላይ ቀንሶ ለአረጋዊያን መንከባከቢያ ማዕከሉ ድጋፍ ማድረጉንና በዚሁ አጋጣሚ በማዕከሉ የሚገኙትን በመጎብኘት ሠራዊቱ ከጎናቸው መሆኑን በተግባር ለማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡ ዘጋቢው ናትናኤል ማሩ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 15:57
t.me/fdredefenseforc/38800
የተንሳኤን በዓል በማሥመልከት ለመከላከያ ሠራዊቱ ሠንጋ እየተበረከተ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

በቄለም ወለጋ ዞን የጊዳሚ ወረዳ አስተዳደር ለመብረቅ ከፍለ ጦር የሰራዊት አባላት የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ 05 የእርድ ሰንጋ ለሠራዊቱ አበርክቷል። ድጋፉን የተረከቡት የመብረቅ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሌተናል ኮሎኔል ንጉሴ ጥላሁን የቄለም ወለጋ ዞን የወረዳ አስተዳደሩ ለሠራዊቱ ያደረገው ድጋፍ ህብረተሰቡ ወገናዊነቱን ያንፀባረቀበት ነው ብለዋል።

ድጋፉን ያስረከቡት የጊዳሚ ወረዳ አስተዳደር አቶ ዋቅ ጋር ደበላ መከላከያ ሠራዊቱ እስከ ህይወት መሰዋዕትነት እየከፈለ የአሽባሪው ኦነግ ሸኔን ሴራ ከአካባቢው ህዝብ ጋር ጥምረት በመፍጠር በማክሸፍ የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና የህዝቧ ደህንነት ተጠብቆ እንዲኖር ያስቻለ መሆኑን ጠቅሰው በግዳጅ ላይ ላለው ሰራዊት ለበዓል መዋያ  የእርድ ሰንጋ አስረክበዋል። ዘገባው የቢኒያም ኤርምያስ ነው።
         
በተመሳሳይ ለዋልያ ክፍለ-ጦር ለትንሳኤ በአል የእርድ ሰንጋዎችን ያበረከቱት የአንፍሎ ወረዳ አስተዳደር አቶ ነጋሽ ቀነዓ ሀገራችን ታፍራና ተከብራ እንድትኖር በዱር በገደሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ህዝብና መንግስት የሰጡትን አደራ ተቀብሎ ግዳጁን እየተወጣ የሚገኘዉ ሰራዊታችን ይህ ድጋፍ ሲያንሠው እንጂ አይበዛበትም ብለዋል። ።

ድጋፉን የተረከቡት የዋልያ መቶ አለቃ ዮናስ ይልማ በበኩላቸው ሰራዊቱ ግዳጅ ለመፈፀም በሚንቀሳቀስባቸው በእያንዳንዱ ቀጠና ተልዕኮውን በሚገባ በመረዳት ህዝባዊ ወገንተኝነቱን በማስቀደም ግዳጁን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። ዘገባው የብሩክ ታደሠ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 13:33
t.me/fdredefenseforc/38794
የሀገራችንን የአየር ክልል ከማንኛውም ጥቃት ከመጠበቅ ባለፈ ታሪክን የማደስ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
   ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢፌዴሪ አየር ሀይል አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ከሰላሳ ሰባት ዓመት በላይ ከአገልግሎት ውጭ ሆኖ የቆየውንና የቀድሞ የሀገራችን ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማሪያም ይንቀሳቀሱባት የነበረው የDHC-5  Buffalo አውሮፕላንን ጥገናና ማሻሻል በማድረግ ወደ ስራ ላስገቡ ኢንጅነሮችና ቴክኒሺያኖች ምስጋና አቅርበዋል።

አውሮፕላኑን ሙሉ ጥገና የተካሄደለትና ከዘመኑ ጋር የተዋሀዱ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙላት መሆኑን ማረጋገጣቸውና በተደጋጋሚ ሙከራ ወደ ሀይል እንዲቀላቀል በመደረጉ መደሰታቸውን የገለፁት አዛዡ ፤ በተቋሙ የሚመራመሩና ተአምር የሚፈጥሩ ወጣቶች መኖራቸውን ያየንበትም ነው ብለዋል።

መከላከያ ትጥቆችን ከመግዛት በተጨማሪ አምራች ለመሆን እያደረገው ባለው ጥረት ከፍተኛ ውጤት እየተገኙ መሆኑን የገለፁት ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ ፤ አንጋፋው የአየር ሀይላችንም የዚሁ አካል በመሆን በተለያዩ ዘርፎች የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።

ለታላቅ ሀገር ፣ ታላቅ የአየር ሀይል በሚል መርህ መሪ ቃል የተገነባው የአየር ሀይላችን የሀገራችንን የአየር ክልል ከመጠበቅ ባለፈ ታሪኩን እያደሰና ዘመኑን የዋጀ ተግባራትን እያከናወነ ሀገራዊ አቅም የመሆን ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል።

በአየር ሀይል ቴክኒሺያኖች ጥገናና መሻሻል ተደርጎላት ወደ ሀይል የተቀላቀለውና የካናዳ ስሪት የሆነው የDHC-5  Buffalo አውሮፕላን የቀድሞ የሀገራችን ፕሬዝዳንት ከሀገር ሲሸሹ እስከ ኬንያ የሄዱበት አውሮፕላን መሆኑ ታሪካዊ ያደርገዋል።

ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ አባቱ ወልደማርያም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 11:38
t.me/fdredefenseforc/38791
የመቻል ሴት እግር ኳስ ቡድን ቂርቆስ ክፍለ ከተማን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

በሃያ ሁለተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ መቻል ቂርቆስ ክፍለ ከተማን ሶስት ለባዶ በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ ነጥብ አስመዝግቧል።

ለመቻል የማሸነፊያ ጎሎቹን ፎዚያ መሐመድ ሁለት እና ስንታየሁ ሂርኮ አንድ አስቆጥረዋል። የዛሬው ድል ተከትሎ የመቻል ሴት እግር ኳስ 36 ነጥብ በመያዝ አምስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችለዋል።

የሴቶች ፕሪምየርሊግ ውድድር በሀዋሳ አርቴፊሻል ስታድየም የሚቀጥል ሲሆን በ23ኛ ሳምንት መቻል ከሀዋሳ ከተማ ተጠባቂ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ዘጋቢ ገረመው ጨሬ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 11:33
t.me/fdredefenseforc/38784
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 11:33
t.me/fdredefenseforc/38783
ለሲኒየር የህክምና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው የሰልጥኖ አሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቀቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

ስልጠናው በውጊያ ወቅት የሚያጋጥሙ ጉዳቶች በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ  ያለመ የሰልጥኖ አሰልጣኞች ስልጠና ነው።

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አዛዥ ኮሎኔል በላቸው ካሳዬ ፣  ጤና ዋና መምሪያው የሰራዊቱን የጤና አገልግሎት ለማሳደግ በየዘርፉ የሚገኙ የህክምና  ባለሙያዎችን ለማፍራትና ለማብቃት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ስልጠናው ሲኒየር የህክምና ባለሙያዎች መሰጠቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የገለፁት አዛዡ በውጊያ ወቅት  የሚያጋጥሙ ጉዳቶችን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ መሆኑን ገልፀዋል።

በሰራዊቱ ውስጥ ለረጅም ጊዜ እያገለገሉ የሚገኙ  የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን ልምዶች በመቀመር ለትውልዱ መማሪያነት ማዋል እንደሚገባቸውም ገልፀዋል።

ሰልጣኞች የሰራዊት የህክምና ባለሙያዎችን በማብቃትና አቅማቸውን በመጨመር የሰራዊታችንን ጤንነት በማረጋገጥና ለግዳጅ ውጤታማነት የበኩላቸውን የመወጣት ተግባራቸውን አጠናክረው መቀጠል እንደሚኖርባቸው ገልፀዋል ።

የስልጠና ሪፖርት ያቀረቡት በጦር ሀይሎች ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የስልጠናና ምርምር  ዳይሬክተር ኮሎኔል ዶክተር አሰማ ተፈራ ፣ ሰልጣኞቹ በዘርፉ የረጅም ጊዜ የስራ ልምድና ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ ያላቸው መሆኑንና በየጊዜው እያደገና እየተሻሻለ የመጣው የህክምና ዘርፍ ላይ ያላቸውን አቅም የጨመረ መሆኑን ተናግረዋል።

በስልጠናው የተገኙ ልምዶችን በተግባር በማዋል በውጊያ ወቅት የሚያጋጥሙ ጉዳቶችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ የሚያስችል አለም አቀፍ ልምዶች የተካተቱበት መሆኑንም ጠቁመዋል።

ስልጠናነው 68 ፐርሰንት  በተግባር 32 ፐርሰንት በንድፈ ሀሳብ መሰጡቱን የገለፁት ዳይሬክተሩ  ሰልጣኞች   ከሰማንያ በላይ ነጥብ ማስመዝገባቸው በምዘና መረጋገጡን ገልፀዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በስልጠናው አዳዲስ ልምዶችን ማግኘታቸው በዘርፉ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን ለመቀነስ አጋዥ መሆኑን ገልፀዋል።

በስልጠናው ባገኙት ዕውቀትም በሙያው ከማገልገል ባለፈ ከህክምና ባለሙያዎች በተጨማሪ ሁሉም የሰራዊቱ አባላት ግንዛቤ ለማስጨበጥ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

ስልጠናው የጤና ሚኒስቴር ከጦር ሀይሎች ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።

ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ አባቱ ወልደማርያም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
04/18/2025, 11:05
t.me/fdredefenseforc/38779
Search results are limited to 100 messages.
Some features are available to premium users only.
You need to buy subscription to use them.
Filter
Message type
Similar message chronology:
Newest first
Similar messages not found
Messages
Find similar avatars
Channels 0
High
Title
Subscribers
No results match your search criteria