O seu período de teste terminou!
Para acesso total à funcionalidade, pague uma subscrição premium
FA
FBC (Fana Broadcasting Corporate)
https://t.me/fanatelevision
Idade do canal
Criado
Linguagem
Amárico
0.18%
ER (semana)
4.34%
ERRAR (semana)

This is FBC's official Telegram channel.

For more updates please visit www.fanabc.com

Mensagens Estatísticas
Repostagens e citações
Redes de publicação
Satélites
Contatos
História
Principais categorias
As principais categorias de mensagens aparecerão aqui.
Principais menções
Não foram detectadas menções significativas.
Encontrado 4 799 resultados
የዕለቱ የውጭ ምንዛሪ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
22.04.2025, 07:56
t.me/fanatelevision/93428
ሊድስ ዩናይትድ እና በርንሌይ ወደ ፕርሚየር ሊጉ አደጉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊድስ ዩናይትድ እና በርንሌይ ለ2025/26 የውድድር ዓመት ከሻምፒዮን ሺፕ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማደጋቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ዛሬ በተደረገ የሻምፒዮን ሺፕ ጨዋታ በርንሌይ ሼፍልድ ዩናይትድን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ በርንሌይ ነጥቡን 94 በማድረስ ለቀጣዩ የውድድር ዓመት ወደ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል።

በተመሳሳይ ሊድስ ዩናይትድ ስቶክ ሲቲን በማሸነፍ ወደ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ያደገ ሌላኛው ቡድን መሆን ችሏል፡፡https://www.fanamc.com/archives/290713
21.04.2025, 21:56
t.me/fanatelevision/93426
21.04.2025, 21:56
t.me/fanatelevision/93427
https://www.youtube.com/watch?v=rIwUp7SBgX4
21.04.2025, 20:48
t.me/fanatelevision/93425
በጅቡቲ ሕጋዊ የመኖሪያ ሰነድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ዜጎች የመመለሻ ጊዜ አልተራዘመም – ኤምባሲው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጅቡቲ ሕጋዊ የመኖሪያ ሰነድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን እና የሌሎች ሀገራት ዜጎች ወደየሀገራቸው የመመለሻ ጊዜ አለመራዘሙን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡ ኤምባሲው÷የጅቡቲ መንግስት ሕጋዊ የመኖሪያ ሰነድ ሳይኖራቸው በሀገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ከፈረንጆቹ ሚያዝያ 3 እስከ ግንቦት 2 ቀን 2025 ባለው ጊዜ ውስጥ በፈቃደኝነት ወደየሀገራቸው እንዲመለሱ ማሳወቁን…

https://www.fanamc.com/archives/290709
21.04.2025, 20:47
t.me/fanatelevision/93424
https://www.youtube.com/watch?v=Yu61-cSgSUs
21.04.2025, 20:20
t.me/fanatelevision/93422
ባሕርዳር ከተማ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባሕርዳር ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የባሕርዳር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ቸርነት ጉግሳ እና አቤል ማሙሽ በተመሳሳይ ሁለት ሁለት ግቦችን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ መቐለ 70 እንደርታን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ አሸናፊ ሀፍቱ አስቆጥሯል፡፡ ውጤቱን…

https://www.fanamc.com/archives/290705
21.04.2025, 20:02
t.me/fanatelevision/93421
https://www.youtube.com/watch?v=6jy8KRS-9lI
21.04.2025, 20:00
t.me/fanatelevision/93420
የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተለያዩ ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ መልዕክት አስፍረዋል፡፡ በተመሳሳይ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የሕንድ…

https://www.fanamc.com/archives/290702
21.04.2025, 18:03
t.me/fanatelevision/93418
17
1
2.2 k
የሰላም ሚኒስቴር በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማውን ሃዘን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰላም ሚኒስቴር በሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ሃዘን ገልጿል። ሚኒስቴሩ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት ከፍተኛ ሃዘን ላይ ለሚገኙት የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ምዕመናን መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

https://www.fanamc.com/archives/290699
21.04.2025, 17:06
t.me/fanatelevision/93417
12
4.5 k
በተደራጀ መረጃ ዓለም አቀፋዊ ተደራሽነትን ማስፋት ያስፈልጋል – አቶ አድማሱ ዳምጠው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተደራጀ መረጃ ዓለም አቀፋዊ ተደራሽነትን ማስፋትይገባል ሲሉ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አድማሱ ዳምጠው ገለጹ፡፡ አቶ አድማሱ በቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ዓለም አቀፍ ዲፓርትመንት አዘጋጅነት ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ የሚዲያ መሪዎች የውይይት መድረክ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው በዚህ ወቅት÷ፈጣንና ዓላማ ተኮር መረጃ…

https://www.fanamc.com/archives/290689
21.04.2025, 15:59
t.me/fanatelevision/93416
40
3
6.8 k
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈተ-ሕይዎት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በሆኑት በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለጹ፡፡

ፓትርያርኩ ለመላው የሮማ ካቶሊካዊ መሪዎች እና በመላው ዓለም ላሉ ምእመናን እንዲሁም በኢትዮጵያ ላሉ ካቶሊካውያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ሐዘናቸውን ገልጸዋል።
21.04.2025, 14:30
t.me/fanatelevision/93415
16
3
6.5 k
ፕሬዚዳንት ታዬ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈተ ሕይዎት የተሰማቸውን ሐዘን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ታዬ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት፤ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈት ጥልቅ ሐዘን ተሰምቶኛል ብለዋል፡፡

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ፤ ለእምነት፣ ለሰብዓዊነት እና ለዓለም አቀፍ ሰላም ማገልገላቸውን አውስተዋል፡፡

ነፍሳቸው በሰላም ትረፍ፤ መታሰቢያነቱም ለዘላለም ይሁን፤ ሲሉም ፕሬዚዳንቱ በሐዘን መግለጫ መልዕክታቸው ገልጸዋል፡፡
21.04.2025, 14:24
t.me/fanatelevision/93414
9
2
6.5 k
የኢትዮ-ፓኪስታን የወዳጅነት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮ-ፓኪስታን የወዳጅነት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) በተገኙበት በሲያልኮት ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ከ1 ሺህ በላይ የሀገሪቱ ተማሪዎች እና የከፍተኛ ትምህርት ማሕበረሰብ አባላት መሳተፋቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡ አምባሳደር ጀማል (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት÷ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተገበረችው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለአየር…

https://www.fanamc.com/archives/290653
21.04.2025, 13:48
t.me/fanatelevision/93413
13
7.0 k
3 ሺህ 285 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 3 ሺህ 285 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ተመላሾቹ 2 ሺህ 747 ወንዶች፣ 508 ሴቶች እና 30 ጨቅላ ሕጻናት ሲሆን÷ ከእነዚህ ውስጥም 159 እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ በ4ኛው ዙር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን የመመለስ ሥራ…

https://www.fanamc.com/archives/290650
21.04.2025, 13:09
t.me/fanatelevision/93412
17
5
7.3 k
በ3 ሀገራዊ ቋንቋዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና እንዲሰጥ ተፈቀደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ እና ሶማልኛ ቋንቋዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና እንዲሰጥ መፈቀዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ባለሥልጣኑ በሪፎርም ሒደት ውስጥ እንደሚገኝ እና ለረጅም ግዜ ሲጠየቁ የነበሩ በርካታ የተገልጋዮቻችን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እየፈታ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ ተቋሙ ከሚሰጣቸው በርካታ አገልግሎቶች ውስጥ አዲስ…

https://www.fanamc.com/archives/290647
21.04.2025, 12:47
t.me/fanatelevision/93410
በ3 ሀገራዊ ቋንቋዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና እንዲሰጥ ተፈቀደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ እና ሶማልኛ ቋንቋዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና እንዲሰጥ መፈቀዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

ባለሥልጣኑ በሪፎርም ሒደት ውስጥ እንደሚገኝ እና ለረጅም ግዜ ሲጠየቁ የነበሩ በርካታ የተገልጋዮቻችን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እየፈታ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

ተቋሙ ከሚሰጣቸው በርካታ አገልግሎቶች ውስጥ አዲስ መንጃ ፍቃድ አገልግሎት አንዱ ሲሆን÷ የእጩ አሽከርካሪዎች የንድፈ ሃሳብ ስልጠና እና ፈተና በአማርኛ ቋንቋ ብቻ ሲሰጥ እንደነበር ተጠቅሷል።

በአፍ-መፍቻ ቋንቋቸው በአማራጭነት ቢሰለጥኑ እና ቢፈተኑ የተሻለ ውጤት ሊያመጡ እንደሚችሉ ለረጅም ጊዜ ሲጠየቅ የነበረ የመልካም አስተዳድር ጥያቄ መሆኑን የባለስልጣኑ መረጃ አመልክቷል፡፡

ይህን ተከትሎም ተቋሙ በዝርዝር ጉዳዩን ፈትሾ የአካታችነት ጥያቄው አሳማኝ መሆኑንና የተሟላ የካሪኩለም ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን በማንሳት ለመንጃ ፍቃድ ስልጠና በ3 ሀገራዊ ቋንቋዎች ስልጠና እንዲሰጥ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በዚህም ፍቃድ ከሰጣቸው 137 ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ከአማርኛ በተጨማሪ በአፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ እና ሶማልኛ ቋንቋዎች ለማሰልጠን ፍቃደኛ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ስለሆነም ሞዴል ተቋማት ለሆኑ 12 ማሰልጠኛ ተቋማት ፍቃድ መሰጠቱ ነው የተጠቆመው፡፡

በሌላ በኩል ዕጩ አሽከርካሪዎች ከአማርኛ በተጨማሪ በቀረቡት የቋንቋ አማራጮች መሰልጠን እና መፈተን እንደሚችሉ ባለስልጣኑ አስገንዝቧል፡፡
21.04.2025, 12:44
t.me/fanatelevision/93409
👉የጠቅላይ ሚኒስትሩ የቬይትናም ጉብኝት

👉የአፈር ማዳበሪያው ነገር
21.04.2025, 12:35
t.me/fanatelevision/93408
17
4
7.4 k
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማትን ሃዘን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማትን ሃዘን ገልጻለች፡፡ ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው የሃዘን መግለጫ÷ ፖፕ ፍራንሲስ ዛሬ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውንና በዚህም ቤተክርስቲያኗ የተሰማትን ሃዘን ገልጻለች፡፡

https://www.fanamc.com/archives/290644
21.04.2025, 12:18
t.me/fanatelevision/93407
13
2
7.5 k
መቻል አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የመቻልን ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ሽመልስ በቀለ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቆ በተጨመረ ደቂቃ እና በ49ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ መቻል በ38 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ አዳማ ከተማ ደግሞ በ21 ነጥብ…

https://www.fanamc.com/archives/290638
21.04.2025, 11:54
t.me/fanatelevision/93405
50
7
7.2 k
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡
21.04.2025, 11:41
t.me/fanatelevision/93404
57
15
7.8 k
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ባደረባቸው ከፍተኛ የሳንባ ሕመም የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይተው በዛሬው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡፡
21.04.2025, 11:14
t.me/fanatelevision/93403
19
3
7.1 k
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌጎስ የሚያርገውን ሳምንታዊ በረራ በእጥፍ አሳደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄርያ ሌጎስ ከተማ እያደረገ ያለውን 7 ሳምንታዊ በረራ ከሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ 14 ሳምንታዊ በረራ አሳደገ፡፡

ይህም ለደንበኞቹ ይበልጥ ምቹ የበረራ አማራጭ መስጠት የሚያስችል መሆኑን አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡
21.04.2025, 11:07
t.me/fanatelevision/93402
13
4
6.9 k
ለ30 ተቋማት ነጻ የዳታ ማዕከል አገልግሎት እየተሰጠ ነው – ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለ30 የመንግስት ተቋማት ነጻ የዳታ ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተ ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) እንዳሉት ÷ በኢትዮጵያ የሚገኙ ተቋማት ዳታን በአግባቡ ጥቅም ላይ የማዋል ልምዳቸው አነስተኛ ነው፡፡ በሌላ በኩል ዳታን በትክክል የማስቀመጡ ተሞክሮ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው÷ያለውን ዳታ ተረድቶ በአግባቡ…

https://www.fanamc.com/archives/290627
21.04.2025, 11:06
t.me/fanatelevision/93401
ፖሊስ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታውቋል፡፡ በዚህም መሠረት ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመከላከል በተደረገ ኦፕሬሽን፤ 121 የጦር መሣሪያዎችን ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች እና 36 የጦር መሣሪያዎችን በኬላዎች ላይ መያዙን ገልጿል፡፡ በተጨማሪም 6…

https://www.fanamc.com/archives/290618
21.04.2025, 10:48
t.me/fanatelevision/93400
21.04.2025, 10:38
t.me/fanatelevision/93399
21.04.2025, 10:38
t.me/fanatelevision/93398
21.04.2025, 10:38
t.me/fanatelevision/93397
21.04.2025, 10:38
t.me/fanatelevision/93396
27
9
6.5 k
ፖሊስ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመከላከል በተደረገ ኦፕሬሽን፤ 121 የጦር መሣሪያዎችን ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች እና 36 የጦር መሣሪያዎችን በኬላዎች ላይ መያዙን ገልጿል፡፡

በተጨማሪም 6 ሺህ 351 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 51 ሺህ 846 በኬላዎች ተይዘዋል መባሉን የፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

እንዲሁም 236 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ካዝናዎች በመኖሪያ ቤቶች እና 148 በኬላዎች ላይ መያዛቸው ተጠቁሟል፡፡

በተመሳሳይ 1 ብሬን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 2 ብሬን በኬላዎች የተያዘ ሲሆን፤ 31 የተለያዩ ቦምቦች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 25 ቦምቦችን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 122 ቦምቦችን በኬላዎች መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

32 የተለያዩ ሕገ-ወጥ ሽጉጦች ከመኖሪያ ቤቶች፣128 ሽጉጦች ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 102 በኬላዎች መያዝ መቻሉንም ጠቅሷል፡፡

1 ስናይፐር ከመኖሪያ ቤቶች እንዲሁም 1 ስናይፐር ከፀረ-ሰላም ኃይሎች በኤግዚቢትነት መያዙን እና 146 ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድቷል፡፡

https://www.fanamc.com/archives/290618
21.04.2025, 10:38
t.me/fanatelevision/93395
18
5
6.8 k
ቬይትናም ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ግንኙነት ኢትዮጵያን እንደበር ትጠቀማለች- ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በእስያ ለምትዳርገው ሁለንተናዊ ግንኙነት ቬይትናምን፤ ቬይትናምም በአፍሪካ ለሚኖራት ግንኙነት ኢትዮጵያን እንደ ስልታዊ አጋር ይጠቀማሉ ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሣምንት በቬይትናም ያደረጉትን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አሥመልክቶ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም፤ ቬይትናም…

https://www.fanamc.com/archives/290605
21.04.2025, 10:27
t.me/fanatelevision/93394
15
4
6.9 k
የምንከተለው የብዝኃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ውጤታማ መሆኑን ከቬይትናም ጉብኝት ተረድቻለሁ- ወ/ሮ ሙፈሪሃት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በቬይትናም ያደረገውን ጉብኝት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም፤ ቬይትናም በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወኗ ከቀውስ አዙሪት በፍጥነት መውጣት የቻለችበትን ሁኔታ አንስተዋል፡፡ ተወዳዳሪ ኢኮኖሚን የመገንባት ተልዕኮ የተሰጠው የሰው ሀብት ልማት ሥራ መሠራቱን አንስተው፤…

https://www.fanamc.com/archives/290612
21.04.2025, 10:24
t.me/fanatelevision/93393
14
3
7.6 k
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቬይትናም ጉብኝት በበርካታ ዘርፎች ልምድ የተቀሰመበት ነው – ቢልለኔ ስዩም

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቬይትናም ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጠናክርና በበርካታ ዘርፎች ልምድ የተቀሰመበት ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ፡፡ ቢልለኔ ስዩም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በቬይትናም ያደረጉትን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

https://www.fanamc.com/archives/290607
21.04.2025, 10:15
t.me/fanatelevision/93392
8
3
8.7 k
ኢትዮጵያን በመጎብኘት በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት ያድርጉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
21.04.2025, 09:38
t.me/fanatelevision/93391
25
3
9.8 k
የዕለቱ የውጭ ምንዛሪ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
21.04.2025, 07:54
t.me/fanatelevision/93390
20.04.2025, 20:30
t.me/fanatelevision/93388
20.04.2025, 20:30
t.me/fanatelevision/93389
20.04.2025, 20:30
t.me/fanatelevision/93387
79
3
13 k
ሌስተር ሲቲ ከእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ሌስተር ሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በኪንግ ፓዎር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሊቨርፑልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አሌክሳንደር አርኖልድ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ሌስተር ሲቲ ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱን ሲያረጋግጥ ሊቨርፑል ደግሞ መሪነቱን ማጠናከር ችሏል፡፡

በዚህም ሌስተር ሲቲ አምስት ጨዋታ እየቀረው ሳውዝሃምፕተንን በመከተል ወደ ሻምፒዮንሺፕ የወረደ 2ኛው ቡድን ሆኗል።

በአንጻሩ ሊቨርፑል ከተከታዩ አርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 13 ከፍ ያደረገ ሲሆን፣ ዋንጫውን ለማንሳት የተቃረበበትን ወሳኝ ድልም አስመዝግቧል።
20.04.2025, 20:30
t.me/fanatelevision/93386
15
2
12 k
https://www.youtube.com/watch?v=CrKvqXj1gMI
20.04.2025, 19:54
t.me/fanatelevision/93385
13
2
12 k
https://www.youtube.com/watch?v=X6AHgdO8xzY
20.04.2025, 18:49
t.me/fanatelevision/93384
17
5
11 k
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በገላን ጉራ ከሚገኙ የካሳንቺስ ልማት ተነሺዎች ጋር የትንሳኤ በዓልን ሲያከብሩ ያስተላለፉት መልዕክት
20.04.2025, 18:43
t.me/fanatelevision/93383
35
2
12 k
አርሰናል ሲያሸነፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከሜዳው ውጪ ኢፕስዊች ታውንን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡ ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኢፕስዊች ታውንን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡ አርሰናል የጨዋታ ብልጫ በወሰደበት ጨዋታ ሊያንድሮ ትሮሳርድ (2)፣ ጋብርኤል ማርቲኔሊ እና ኢታን ኒዋኔሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል።…

https://www.fanamc.com/archives/290596
20.04.2025, 18:12
t.me/fanatelevision/93382
19
3
10 k
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን ከኮሪደር ልማት ሰራተኞች አከበሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን ከካዛንቺስ ኮሪደር ልማት ሰራተኞች፣ ኮንትራክተሮች እና አማካሪዎች ጋር የትንሳዔ በዓልን አክብረዋል። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰራተኞችን በማበረታት እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፤ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል። የኮሪደር ልማት ሰራተኞች ቀን…

https://www.fanamc.com/archives/290593
20.04.2025, 18:10
t.me/fanatelevision/93381
ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከጤና ባለሙያዎችና ታካሚዎች ጋር የትንሳዔ በዓልን አከበሩ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት የጤና አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ባለሙያዎች እና ታካሚዎች ጋር የትንሳዔ በዓልን አክብረዋል። ዶ/ር መቅደስ ዳባ÷ ታካሚዎችን በበዓላት ወቅት ማከም ትልቅ ደስታ እንደሚፈጥር ጠቅሰው፣ የጤና ሙያ ራስን…

https://www.fanamc.com/archives/290588
20.04.2025, 18:07
t.me/fanatelevision/93380
5
2
11 k
https://www.youtube.com/watch?v=zWkTxvlGNZM
20.04.2025, 17:29
t.me/fanatelevision/93379
29
2
11 k
ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ 26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። የሊጉ ጨዋታ አመሻሽ 12 ሠዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ አርባ ምንጭ…

https://www.fanamc.com/archives/290583
20.04.2025, 17:13
t.me/fanatelevision/93378
29
4
11 k
ዛሬ ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርተናል - ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው
20.04.2025, 16:54
t.me/fanatelevision/93377
የተለወጠችና ከልመና የወጣች ሀገር እውን ከማድረግ ውጪ ሌላ ሃሳብ የለንም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተለወጠችና ከልመና የወጣች ሀገር እውን ከማድረግ ውጪ ሌላ ሃሳብ የለንም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ የትንሳኤ በዓልን በገላን ጉራ ከሚገኙ የካሳንቺስ ልማት ተነሺዎች ጋር አሳልፈናል ብለዋል። ጎስቋላ የነበረውን ከተማ እንቀይረው ያልነው ለጋራ ጥቅም፣ ለልጆቻችን ደስታ እና…

https://www.fanamc.com/archives/290565
20.04.2025, 14:43
t.me/fanatelevision/93376
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93375
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93371
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93367
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93368
70
2
10.0 k
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የትንሳኤ በዓልን በገላን ጉራ ከሚገኙ የካሳንቺስ ልማት ተነሺዎች ጋር አሳልፈናል።

ጎስቋላ የነበረውን ከተማ እንቀይረው ያልነው ለጋራ ጥቅም፣ ለልጆቻችን ደስታ እና መጻኢውን ዘመን ለማሳመር ብቻ ነው።

የተለወጠችና ከልመና የወጣች ሃገር እውን ከማድረግ ውጪ ሌላ ሃሳብ የለንም።

ይህ አዲሱ ሰፈራችሁ የምትኖሩበት ነው። ቀድሞ የኖራችሁበት ሰፈራችሁን ሄዳችሁ እንድታዩት እጋብዛለሁ።

ቃል በገባነው መሰረት ካሳንቺስ እጅግ ውብ ሆኗል። ልጆቻችን ተስፋ አላቸው ፣ ከእኛ የተሻለ ህይወት መኖር ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ትንሳኤ ቅርብ ነው። እኛም እናያለን፣ ልጆቻችንም ይወርሳሉ።
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93366
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93370
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93373
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93374
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93369
20.04.2025, 14:13
t.me/fanatelevision/93372
31
6
10 k
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያደረጉት ማዕድ ማጋራት።
20.04.2025, 13:44
t.me/fanatelevision/93365
17
3
11 k
ማስታወቂያ

እጥፍ ወለድ....
********
ከባህር ማዶ ለበዓል ገንዘብ ሲላክልዎ፤
የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ ይክፈቱ!

• ከመደበኛው ሂሳብ እጥፍ ወለድ ያስገኛል ፣
• ለውጭ ሀገር ጉዞዎ ቅድሚያ የውጪ ምንዛሬ ያገኛሉ፡፡

ከወዲሁ መልካም የትንሣኤ በዓል እንመኝልዎታለን!
********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#CBE #saving #foreigncurrency #banking #ethiopia #easter
20.04.2025, 12:39
t.me/fanatelevision/93364
33
4
9.8 k
ጊዜያዊ ችግሮቻችንን በመረዳዳት እየተሻገርን ለዘላቂ ልማታችን በመስራት የኢትዮጵያን ብልጽግና እናረጋግጣለን – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጊዜያዊ ችግሮቻችንን በመረዳዳት እየተሻገርን ለዘላቂ ልማታችን በመስራት የኢትዮጵያን ብልጽግና እናረጋግጣለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ 25ኛውን እና 26ኛውን የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል አገልግሎት ማስጀመራቸውን አስታውቀዋል። ከ2014 ጀምረን በቀን አንድ ጊዜ እንኳን…

https://www.fanamc.com/archives/290558
20.04.2025, 12:06
t.me/fanatelevision/93363
30
6
10.0 k
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 25ኛውን ተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ 25ኛውን ተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ጉራራ ቅርንጫፍ መርቀው ስራ አስጀምረዋል። ከንቲባዋ በአዲሱ ማዕከል የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞችና ለተለያዩ ማህበራዊ ችግርች ለተጋለጡ ወገኖች ማዕድ አጋርተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት÷ ከተማ አስተዳደሩ ከግሉ ዘርፍ ጋር በመተባበር የምገባ…

https://www.fanamc.com/archives/290555
20.04.2025, 11:03
t.me/fanatelevision/93362
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93361
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93358
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93359
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93360
37
3
9.2 k
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያደረጉት ማዕድ ማጋራት በምስል፡-
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93352
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93357
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93353
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93355
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93354
20.04.2025, 10:18
t.me/fanatelevision/93356
20.04.2025, 10:12
t.me/fanatelevision/93350
20.04.2025, 10:12
t.me/fanatelevision/93348
20.04.2025, 10:12
t.me/fanatelevision/93349
20.04.2025, 10:12
t.me/fanatelevision/93351
24
3
7.8 k
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርተዋል።
20.04.2025, 10:12
t.me/fanatelevision/93347
15
2
8.5 k
የተለያዩ ሀገራት ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች እና አምባሳደሮች የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት ለክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በዓሉ የሰላም እና የደስታ እንዲሆን በመመኘት÷ የበዓል ወቅት ለኢትዮጵያውያን ጤና፣ ሰላም እና ተስፋን ይዞ እንዲመጣ እምነት አለኝ ብለዋል። በኢትዮጵያ…

https://www.fanamc.com/archives/290548
20.04.2025, 10:06
t.me/fanatelevision/93346
18
2
10 k
የትንሣኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትንሣኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል። በዓሉን በማስመልከት የሃይማኖት አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት በዓለ ትንሣኤ የእግዚአብሔር ፍቅር መገለጫና የተስፋችን ማሳያ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል ብለዋል። በዓለ ትንሣኤውን ስናከብርም ለእግዚአብሄር ክብርና ለሰው ልጆች ደኀንነት በአንድነት በመቆም መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የትንሣኤ በዓል የክርስቶስን መነሣት ያስተማረን የምሥራች መሆኑንም…

https://www.fanamc.com/archives/290544
20.04.2025, 08:54
t.me/fanatelevision/93344
24
5
9.1 k
የበዓል ወቅት አመጋገብ ጥንቃቄ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የበዓላት ወቅት አመጋገብ ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገበት ለጤና ችግር ሊዳርግ እንደሚችል የጤና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በመሆኑም የበዓላት ወቅት አመጋገብን ጥንቃቄ የተሞላበት ማድረግ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ ምክንያቱም ቅባት የበዛበት ምግብ መመገብ ጨጓራን ለህመም የመዳረግ ዕድሉ ከፍተኛ ስለሚሆን ነው ይላሉ፡፡ ጥንቃቄ የጎደለው አመጋገብ ከሆነ÷ እንደ ሆድ መንፋት፣ የሆድ ቁርጠት፣ የጨጓራ…

https://www.fanamc.com/archives/290540
20.04.2025, 07:15
t.me/fanatelevision/93342
22
9.1 k
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት በጾም በጸሎት ያሳለፉ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን አስፈሰኩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት በጾም በጸሎት ያሳለፉ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች፣ አካል ጉዳተኞች እና ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖችን አስፈስከዋል። ፆም የምናስፈታው በባህላችን መሰረት ሌሎች ፆም በሌሊት ሲፈቱ እና በዓሉን በድምቀት ሲያከብሩ ጠያቂ የሌላቸው አረጋውያን፣ የሀገር ባለውለታዎች እና ለተለያዩ ማህበራዊ…

https://www.fanamc.com/archives/290537
20.04.2025, 07:13
t.me/fanatelevision/93341
23
1
9.7 k
ሞት ድል የሆነበት ትንሣኤ!

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የትንሣኤ በዓል እየተከበረ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል መምህራን እንደሚሉት፤ ትንሣኤ ምዕመኑ መከባበርና አንዱ ለአንዱ መልካም ማድረግን የሚማርበት ዐውድም ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን አስተምኅሮ ክርስቲያኖች በዓለ ትንሣኤን የሚያከብሩበት ዐውድ እና የሚገልጹበት ሃይማኖታዊ መስተጋብሮች እጅግ ብዙ መሆናቸውን በማንሳት፤ ከእነዚህ መካከል…

https://www.fanamc.com/archives/290534
20.04.2025, 07:10
t.me/fanatelevision/93340
32
3
11 k
https://youtu.be/lIa1JpvtriI?si=48CPNxJDYn1Au-Hi
19.04.2025, 22:28
t.me/fanatelevision/93338
20
3
11 k
https://www.youtube.com/watch?v=JdC8AaZ3HfM
19.04.2025, 21:30
t.me/fanatelevision/93337
32
4
11 k
https://www.youtube.com/watch?v=xvvK8Yg7ikg
19.04.2025, 20:20
t.me/fanatelevision/93336
17
3
10 k
ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች፤ ቢንያም ፍቅሩ (2) እና አብዱ ሳሚዮ ሲያስቆጥሩ፤ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ከሽንፈት ያልታደገች ብቸኛ ግብ ደግሞ ቡልቻ ሹራ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ፈረሰኞቹ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ…

https://www.fanamc.com/archives/290527
19.04.2025, 20:02
t.me/fanatelevision/93335
ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች፤ ቢንያም ፍቅሩ (2) እና አብዱ ሳሚዮ ሲያስቆጥሩ፤ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ከሽንፈት ያልታደገች ብቸኛ ግብ ደግሞ ቡልቻ ሹራ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ፈረሰኞቹ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል የተመለሱበትን ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ34 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ11 ነጥብ ወራጅ ቀጠና 18ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
19.04.2025, 20:01
t.me/fanatelevision/93332
19.04.2025, 20:01
t.me/fanatelevision/93334
19.04.2025, 20:01
t.me/fanatelevision/93333
22
6
9.6 k
https://www.youtube.com/watch?v=teR_MDm-uJM
19.04.2025, 19:22
t.me/fanatelevision/93331
42
2
9.7 k
በዓሉን ስናከብርን በአቅማችን በመረዳዳት ይሁን- ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ ለመላው የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም፤ በየዓመቱ የምናከብረው የትንሳኤ በዓል ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ደኅንነት እስከ መስቀል ሞት ታዞ፣ ሞትን አሸንፎ፣ የሰው ልጆችን ወደ ብርሃን ያሻገረበት ታላቅ በዓል ነው ብለዋል፡፡

ይህን በዓል ስናከብርም የተከፈለልንን የፍቅር ዋጋ በማሰብ ድጋፍ ለሚሹ የማሕበረሰብ ክፍሎች በመድረስ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት፡፡

በዚህም ሕጻናትን፣ አረጋውያንን እና ሌሎች የማሕበረሰብ ክፍሎችን በማገዝ፤ በአቅማችን ልክ በመረዳዳት እና በመተሳሰብ በዓሉን እናክብር ብለዋል፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአብሮነት እንዲሆንም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
19.04.2025, 19:11
t.me/fanatelevision/93330
8
2
8.4 k
የትንሳኤ በዓል የፍቅርና የይቅርታ እንዲሆን ብልጽግና ፓርቲ መልካም ምኞቱን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልጽግና ፓርቲ በነገው ዕለት ለሚከበረው የትንሳኤ በዓል ለክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላለፈ፡፡ በመልዕክቱም፤ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብሏል፡፡ በዓሉ፤ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳት፣ የአብሮነት፣ የፍቅርና የይቅርታ እንዲሆንም መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡

https://www.fanamc.com/archives/290508
19.04.2025, 19:06
t.me/fanatelevision/93329
19.04.2025, 19:01
t.me/fanatelevision/93328
24
1
7.7 k
ማንቼስተር ሲቲ ኤቨርተንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኦ-ሬልይ እና ኮቫቺች ማስቆጠር ችለዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ በ58 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ ኤቨርተን በ38 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር፤ ብሬንትፎርድ በሜዳው ብራይተንን አስተናግዶ 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የብሬንትፎርድን የማሸነፊያ ግቦች ምቤሞ (2) ዊሳ እና ኖርጋርድ ሲያስቆጥሩ፤ ለብራይተን ደግሞ ዳኒ ዌልቤክ እና ሚቶማ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ዌስትሀም ዩናይትድ በሜዳው አስቀድሞ መውረዱን ካረጋገጠው ሳውዝሃምፕተን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ሲያጠናቅቅ፤ ክሪስታል ፓላስ እና ቦርንመዝ ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 ተጠናቅቋል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ምሽት 1 ሠዓት ከ30 ሲቀጥል አስቶን ቪላ ከኒውካስል ዩናይትድ በቪላ ፓርክ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
19.04.2025, 19:01
t.me/fanatelevision/93326
19.04.2025, 19:01
t.me/fanatelevision/93327
9
5
9.3 k
https://www.youtube.com/watch?v=xgkEau27i9A
19.04.2025, 18:23
t.me/fanatelevision/93324
27
1
9.5 k
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ለትንሳዔ በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

“እንኳን ለጌታችን፣ ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የተስፋ ብርሃን፣ የመሻገር፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የበጎነት፣ የኅብረትና የአንድነት ይሁንልን። ከሕመሙና ስቃዩ ተሻግሮ ትንሣኤ ያወረሰን ጌታ፤ በሀገራችን፣ በቤታችን ሐሤት፣ ሰላምና በረከት ያብዛልን !! መልካም በዓል !!”

https://www.fanamc.com/archives/290496
19.04.2025, 17:27
t.me/fanatelevision/93323
21
8.8 k
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ለትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

“ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን:: በዓሉ በትንሳዔው ፍቅር፣ በጎነት፣ ደስታ እና ሰላም የተሞላ ይሁንልን:: ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ:: መልካም በዓል!!”

https://www.fanamc.com/archives/290489
19.04.2025, 17:15
t.me/fanatelevision/93322
22
2
8.2 k
በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ኤምባሲዎች ለትንሳዔ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትንሳዔ በዓልን አስመልክቶ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ኤምባሲዎች ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ የብሪታኒያ፣ አሜሪካ፣ ሩሲያ፣ ጀርመን፣ አውስትራሊያ እንዲሁም የፓኪስታን ኤምባሲዎች በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን ተመኝተዋል። ከኤምባሲዎቹ በተጨማሪ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በዓሉን አስመልክቶ…

https://www.fanamc.com/archives/290486
19.04.2025, 17:11
t.me/fanatelevision/93321
Os resultados da pesquisa são limitados a 100 mensagens.
Esses recursos estão disponíveis apenas para usuários premium.
Você precisa recarregar o saldo da sua conta para usá-los.
Filtro
Tipo de mensagem
Cronologia de mensagens semelhante:
Data, mais novo primeiro
Mensagens semelhantes não encontradas
Mensagens
Encontre avatares semelhantes
Canais 0
Alta
Título
Assinantes
Nenhum resultado corresponde aos seus critérios de pesquisa